AM/Prabhupada 0347 - ከሞት በኋላ ፃድቃን በመጀመሪያ ደረጃ ክርሽና ወደሚገኝበት ፕላኔት ውስጥ የወለዳሉ፡



Lecture on BG 2.14 -- Mexico, February 14, 1975

ህርዳያናንዳ፡ የራሳችንን መንፈስ ንፁህ በማድረግ ከአብዩ የመለእክት ጌታ ጋር ያለንን ግኑኝነት እንዲሰማን ማድረግ እንችላለንን?"

ፕራብሁፓድ፡ አዎን የንጽህናም ማእከሉ ይኅው ነው፡፡

ህርዳያናንዳ፡ (የስፔይን ቋንቋ)

ሀኑማን፡ ፕራብሁፓድ እኔለማወቅ የምፈልገው ነገር ቢኖር በመንፈሳዊ ዓለም ውስጥ መወለድ የሚባል ነገር አለ ወይ? ወደ መንፈሳዊ ዓለምስ እንዴት አድረገን ነው የምንገባው?

ፕራብሁፓድ፡ መወለድ ማለት በመጀመሪያ ደረጃ አሁን ክርሽና በአለበት ፕላኔት ውስጥ መወለድ ይኖርብሀል፡፡ ክርሽና በአንዱ ዩኒቨርስ ውስጥ ይገኛል፡፡ ከቁጥር በላይ የሚሆኑ ትእይንተ ዓለሞች ይገኛሉ፡፡ ስለዚህ በመጀመሪያ ደረጃ ክርሽና በአሁኑ ሰዓት በሚገኝበት የትእይንተ ዓለም ውስጥ መወለድ ይገባናል፡፡ በዚህም ትውልድ ሙሉ ልምምድ እናገኛለን፡፡ ከዚህም በኋላ ግን እኛው እራሳችን ወደ ቫይኩንትሀ ፕላኔቶች እንሄዳለን፡፡ መወለድ የሚባል ነገር የለም፡፡ ይህ ምንድነው?

ህርዳያናንዳ፡ ሌላ ጥያቄ እና መልሶች?

ፕራብሁፓድ፡ ካስፈለገ መቀጠል እችላለሁ፡፡

ህርዳያናንዳ፡ ወደ አብዩ ጌታ ለመሄድ ሌላ የተለየ መንገድ አለ? ሌላ መንገድ ካለ፡፡

ፕራብሁፓድ፡ የለም (ሳቅ) ምክንያቱም በብሀገቨድ ጊታ ውስጥ ተጠቅሷል፡፡ “ብሀክትያ ማም አብሂጃናቲ ያቫን ያሽ ቻስሚ ታትቫታሀ ታቶ ማም ታትቫቶ ግያትቫ ቪሻቴ ታድ አናንታራም” (ብጊ፡ 18.55) ስለዚህም ማወቅ ይኖርባችኋል፡፡ “ብሃክትያ ማም አብሂጃናቲ”

ህርዳያናንዳ፡ “ብሀክትያማም አብሂጃናቲ ያቫን ያሽ ቻስሚ ታትቫታሀ ታቶ ማም ታትቫቶ ግያትቫ ቪሻቴ ታድ አናንታራም”

ፕራብሁፓድ፡ ብሀክታ ሳይሆኑ ማንም ወደ መንፈሳዊው የአብዩ ጌታ ቤተ መንግስት ሊገባ አይችልም፡፡ ብሀክታ ለመሆን ደግሞ ምንም ዓይነት ችግር የለም፡፡ ብሀክታ ለመሆነ አራት መመሪያዎችን መከተል ያስፈልጋል፡፡ በመጀመሪያ ደረጃ ክርሽናን ሁሌ ማስታወስ ያስፈልጋል፡፡ “ማን ማና ብሀቫ ማድ ብሀክቶ” ይህ ብሀክታ ይባላል፡፡ ክርሽናን በቀላሉ በማስታወስ ብቻ፡፡ ይህም ሀሬ ክርሽናን በመዘመር ነው፡፡ የክርሽናን ቅዱስ ስም በመዘመር “ሀሬ ክርሽና” ክርሽናን ለማስታወስ እንችላለን፡፡ በዚህም ስርዓት ወዲያውኑ ብሀክታ ለመሆን እንችላለን፡፡ “ማን ማና ብሀቫ” ከሆንክም በኋላ ማድ ያጂ ወይንም እኔን “ስገድልኝ” ማም ናማስኩሩ “የክብር እጅን ንሳ” ይህም በጣም ቀላል ነው፡፡ ክርሽናን የምናስታውስ ከሆነ እና የምንሰግድለት እና እጅ የምንነሳለት ከሆነ እነዚህ ሶስት ነገሮች ብሀክታ ሊያደርጉን ይችላሉ፡፡ በዚህም ስርዓት ወደ አብዩ የመላእክት ጌታ መንፈሳዊ ዓለም ለመሄድ እንችላለን፡፡ ይህንንም እያስተማርን እንገኛለን፡፡ የሀሬ ክርሽናን ቅዱስ ስም ዘምሩ ለክርሽናም እጅ ንሱ የክርሽናንም ሙርቲ ስገዱለት፡፡ በዚህም መንገድ ሁሉን ነገር መጨረስ ትችላላችሁ፡፡

ህርዳያናንዳ፡ (የስፔይን ቋንቋ)

ፕራብሁፓድ፡ ይህ የቀለለ ሆኖ ለምን ወደ ግያና (የእውቀት) መንገድ መሄድ ያስፈልጋል? ይህም ብዙ እውቀት ያስፈልገዋል፡፡ ብዙ የግራመር ጥናት ብዙ ትኩረት እና ሌላ ነገሮችም ያስፈልገዋል፡፡ እነዚህን ሁሉ ነገሮች በማስወገድ እና የተገለጹትን ሶስቱን ብቻ በመከታተል አንድ ሰው ብሀክታ መሆን ይችላል፡፡ ታድያ ይህንን የመሰለ ቀላል መንገድ እያለ ለምን ይህንን በመከተል ወደ ቤታችን ወደ አብዩ ጌታ ቤተ መንግስት አንመለስም? እናመሰግናለን፡፡