AM/Prabhupada 0002 - የእብድ ስልጣኔ፡፡

Revision as of 12:53, 18 October 2018 by Vanibot (talk | contribs) (Vanibot #0023: VideoLocalizer - changed YouTube player to show hard-coded subtitles version)
(diff) ← Older revision | Latest revision (diff) | Newer revision → (diff)


Lecture on SB 6.1.49 -- New Orleans Farm, August 1, 1975

ሀሪ ኬሽ: ትርጉም "ህልም የሚያልም ስው: በህልሙ በሚታየው ገላ እንደሚቀሳቀስ ሁሉ"፣ "ወይንም የሚያየውን ገላ የእኔ ገላ ብሎ እንደሚቀበለው ሁሉ", እንደዚሁም በተመሳሳይ:አሁን ያለውን ገላ የኔ ነው ብሎ ያስባል: ይህም ገላ የተመሰረተው: ከትውልድ በፊት በነበረን ሀይማኖታዊ ወይም ፀረ ሃይማኖታዊ ኑሮ ነው: ያለፈውንም ቢሆን የወደፊቱን ገላ ለማወቅም ያዳግተዋል: ፕራብሁፓዳ (ሽ:ባ: 6.1.49): ያትሃግናስ ታማሳ (ዩክታ) ኡፓስቴ ቭያክታም ኤቫ ና ቬዳ ፑርቫም አፓራም ናስታ ጃንማ ስምርቲስ ታትሃ ይህ የእኛ ስፍራ ነው:: ይህ የእኛ "የሳይንስ እርምጃ" ብለን የምናወራው ነው ከመወለዳችን በፊት: ምን እንደነበርን እንኳን አናውቅም:: ከሞትም በኋላም ምን እንደምንሆን አናውቅም:: ሕይወት የምትቀጥል ናት:: ይህ የመንፈሳዊ ትምህርት ነው:: ሳይንቲስቶች ህይወት እንደምትቀጥል እንኳን አይረዱም:: እንዲያው "በእድል" ይህንን ሕይወት ያገኙ እና ከሞትበኋላ የሚያከትም ይመስላቸዋል:: ከትውልድ በፊት: የአሁን ግዜ: ወይንም የወደፊት ብሎ ነገር የለም እና: አሁን መጨፈር ብቻ ነው: ብለው ያስባሉ:: ይሄ ድንቁርና ይባላል:: "ታማሳ" ሀላፊነት የማይስማው ኑሮ ነው:: እና "አግያ" አግያ ማለት: ዕውቀት የሌለው ስው ማለት ነው:: እና ማነው ዕውቀት የሌለው? "ታማሳ" ማለት ድንቁርና ውስጥ ያሉ ስዎች ማለት ነው:: በአለም ላይ ሶስት አይነት ፍጥረቶች አሉ: "ሳትቫ" "ራጃ" "ታማስ" "ሳትቫ ጉን" ማለት: ሁለ ንጹህ ማለት ነው:: "ፕራካሽ" አሁን እንደምናየው ስማዩ በደመና ተሸፍኗል:: ፀሀይ ግልጽ አደለችም:: ከደመናው በላይ ግን: ፀሀይ በግልፅ አለች:: ሁሉ ነገር ግልፅ ነው:: በደመናው ውስጥ ግን: ሁሉም ግልፅ አይደለም:: እንደዚሁም ሁሉ: የ "ሳትቫ ጉን" ፍጥረት ያላቸው: ለነሱ ሁሉም ነገር ግልፅ ነው:: የ "ታማ ጉን" ፍጥረት ያላቸው ደግሞ: በድንቁርና ውስጥ ናቸው:: ከሁለቱም ደግሞ ሳይሆኑ: የተደባለቁ: ወይ ከ "ሳትቫ ጉን" ወይ "ታማ ጉን" ሳይሆኑ: ማእከለኛዎች: "ራጃ ጉን" ይባላሉ:: ሶስት "ጉናዎች" "ታማስ" ምኞታቸው ሁሉ: ይህንን የያዙትን ገላ መደሰት ብቻ ነው:: ለወደፊት ምን ስለሚመጣ: ምንም ግድ አይሰጣቸውም:: ከትውልድም በፊት ምን እንደነበሩ ምንም እውቀት የላቸውም:: ከዚህ አለም ሌላ እንዳለ ግን በደንብ አድርጎ ተገልጿል:: "ኑናም ፕራማታህ ኩሩቴ ቪካርማ" (ሽ:ባ: 5.5.4) "ፕራማታህ" ልክ እንደ እብድ ሰው:: ለምን እብድ እንደሆነ አያውቅም:: ረስቶታል:: ለሚሰራው ስራ ሁሉ: ከሞት በኋላ ምን እንደሚገጥመው ሁሉ: ምንም አያውቅም:: "እብድ" እና ይሄ ያሁኑ ዘመናችን ስልጣኔ የምንለው: "የእብድ: ስልጣኔ ነው:: ከትውልድ በፊት ስለነበረው ኑሮ ምንም እውቀት የላቸውም:: ከሞት በኋላ ስለአለውም ኑሮ ምንም ግድ አይሰጣቸውም:: "ኑናም ፕራማታህ ኩሩቴ ቪካርማ (ሽ:ባ: 5.5.4) ከትውልድ በፊት ስለነበረው ኑሮ እውቀት ስለሌላቸውም: አሁን ሃጥያት በተሞላ ኑሮ ውስጥ ተሳትፈው ይገኛሉ:: ልክ እንደ ውሻ:: ውሻ ለምን ውሻ እንደሆነ ምንም እውቀት የለውም:: ከሞት በኋላም ምን እንደሚሆን አያውቅም:: ከትውልዱ በፊት: ውሻ: ጠቅላይ ሚኒስቴር ሁኖ ሊሆን ይችላል:: ነገር ግን: ውሻ: ሁኖ ሲወለድ: ምን እንደነበረ ይረሳል:: ይህ "ማያ" የሚባለው የአምላክ ሽፋን ነው:: "ፕራክሴፓትሚካ ሻክቲ: አቫራናትሚካ ሻክቲ" "ማያ" ሁለት አይነት ኅይል አላት:: አንድ ሰው: ከትውልድ በፊት በነበረው የሃጥያት ስራ ምክንያት: ውሻ ሁኖ ቢወለድ: ውሻም ሁኖ ተወልዶ: ከዚህ በፊት ጠቅላይ ሚኒስቴር መሆኑን ቢያስታውስ ይህን እውቀት ይዞ ለመኖር በጣም ያዳግተዋል:: በዚህም ምክንያት: የአምላክ "ማያ" እውቀቱን ትሸፍነዋለች:: "ምርትዩ" ምርትዩ ማለት (ሞት) ሁሉንም ነገር መርሳት ማለት ነው:: ያም "ምርትዩ" (ሞት) ይባላል:: ስለዚህም: ቀንና ሌሊት የማየት ብዙ ልምድ አለን:: ማታ ማታ: በህልማችን የተለየ ቦታ እና የተለየ ህይወት አለን:: በህልም ግዜ ስለ አሁኑ ገላችን ፈጽሞ እንረሳለን:: ለእንቅልፍ መጋደማችንም እንረሳለን:: ገላችን እንደተጋደመ እና ጥሩ አፓርታማ ውስጥ እንዳለን እና ጥሩ የአልጋ ሽፋን እንዳለን እንረሳለን ለምሳሌ በህልሙ መንገድ ላይ ሊራመድ ወይንም ኮረብታ ላይ ሁኖ ሊሆን ይችላል:: በህልሙ የፈለገውን ይዋስዳል: ይዋስዳል:: ሁላችንም: ይህ የህልም ገላ በጣም ይስበናል:: ቀድሞ የነበረንን ገላ እንረሳለን:: እና ይህም ማለት: ድንቁርና ማለት ነው:: "ድንቁርና ማለት ነው" ከዚህ ድንቁርና ደግሞ ከፍ ብለን በእውቀት ከወጣን: ህይዋታችን በለፀገ ማለት ነው:: እራሳችንን በድንቁርና ካስቀረነው: ያም ውድቀት ማለት ነው:: ህይወታችንንም ማበላሸት ማለት ነው:: ይህ የእኛ የክርሽና ንቃት እንቅስቃሴ: የሰው ልጅን ከድንቁርና ወደ እውቀት ለማሸጋገር የሚጥር ድርጅት ነው:: የ "ቬዲክም" ስነፅሁፍም አላማ ይኅው ነው:: የሰው ልጅን ለማዳን:: ጌታ ክርሽናም በ "ብሃገቨድ ጊታ" ቅዱስ መፅሃፍ ስለሁሉም ሳይሆን ስለ አገልጋዮቹ ተናግሯል:: "ቴሻም አሃም ሳሙድሃርታ ምርትዩ ሳምሳራ ሳጋራት" (ብ ጊ 12.7) ሌላው: (ብ ጊ 10.11) "ቴሻም ኤቫኑ ካምፓርትሃም አሃም አግናና ጃም ታማሃ: ናሻያሚ አትማ ባሃቫ ስትሆ ግናና ዲፔና ብሃስቫታ:: ክርሽና: በሁሉም ልብ ውስጥ ተቀምጦ ይገኛል:: ክርሽናን ለማወቅ የሚጥር አገልጋይ: ክርሽና ሁልግዜ ይራዳዋል:: እሱ ይረዳዋል: አጋልጋይ ያልሆኑት ደግሞ: ምንም ግድ አይሰጣቸውም:: ምኞታቸው ሁሉ: እንደ እንስሳ: መብላት: መተኛት: በግብረ ስጋ መገናኘት እና እራሳቸውን መከላከል ብቻ ነው:: ስለ ፈጣሪ ለማዋቅም ሆነ: ወይንም ከፈጣሪ ጋር ያላቸውን ግኑኝነት ለማወቅ: ምንም ግድ አይሰጣቸውም:: እንዲያውም ፈጣሪ የለም ብለው ያስባሉ:: ስለዚህም: ክርሽና: ፈጣሪ እንደሌለ አርገው እንዲያስቡ እና እንዲተኙ: ያደርጋቸዋል:: ስለዚህም "ሳት ሳንጋ" ያስፈልጋል:: ይህ "ሳት ሳንጋ ሳታም ፕራሳንጋት" ከአጋልጋዮች ጋር በመጎዳኘት: ስለ አምላክ ያለንን የመየጠየቅ ጉጉት ለማነቃቃት ያበቃንል:: ስለዚህም የቅርንጫፎቹ መኖር: አስፈላጊ ነው:: ብዙ ቅርንጫፎች የምንከፍተው: አላስፈላጊ ሁኖ እያለ አይደለም:: ቅርንጫፎቹ ለሰው ልጅ ህብረተሰብ: በጥቅም ላይ የሚውሉ ናቸው::