AM/Prabhupada 0007 - የክርሽና እንክብካቤ ይመጣል፡፡

The printable version is no longer supported and may have rendering errors. Please update your browser bookmarks and please use the default browser print function instead.


Lecture on SB 1.5.22 -- Vrndavana, August 3, 1974

ብራህማናንዳ: "ብራህማና (ቄስ) ስራ መቀጠር አይገባውንምን?" ፕራብሁፓዳ: በርሃብ ይሞታታል እንጂ የስራ ቅጥረኝነትን አይቀበልም:: ይህ የብራህመና ባህርይ ነው:: ሻትርያም ሆነ ቫይሻዎች እንዲሁ ናቸው:: ሹድራ ብቻ ነው የሚቀጠረው:: ቫይሻ የራሱን ንግድ ይጀምራል:: የራሱን ንግድ ይፈልጋል:: ለዚህም አንድ ተግባራዊ ምሳሌ አለ:: ከረጅም ግዜ በፊት: በካልካታ ውስጥ: አንድ አቶ ናንዲ የሚባል: ሰው ነበረ:: ወደ ጓደኞቹም ሂዶ እንዲህ አላቸው:: "እናንተ ትንሸ ሀብት ብትሰጡኝ: አንድ ንግድ እጀምር ነበረ::" እንዲህም አለ "እናንተ ቫይሻ ናችሁን? ነጋዴዎች?" "በእርግጥ" "ገንዘብ ከእኔ እየጠየክ ነውን? ገንዘብ መንገድ ላይ ታገኛለህ:: ሂድ እና ታየዋለህ::" እና እሱም እንዲህ አለ:: " አላገኘሁም" "አላገኘሁም? ያስ ምንድን ነው?" "ያ የሞተ አይጥ ነው::" "እንግዲያው ያ ነው ያንተ ሀብት" ይኅውላችሁ: በዚንግዜ: በካልካታ ውስጥ በአይጥ የተነሳ ተላላፊ በሽታ ጀምሮ ነበረ:: የከተማው ማዘጋጃ ቤትም: አዋጅ አውጆ ነበር:: ይህም የተገደለ አይጥ ይዞ ያመጣ ሰው: ሁለት አናስ ይከፈው ነበር:: ስለዚህም ይህ ሰው: የሞተውን አይጥ ይዞ ወደ ማዘጋጃው ጽህፈት ቤት ሄደ:: እዚያም ሁለት አናስ ተከፈለው:: እርሱም ሁለት ቀኑ ያለፈ ቤትል ነትስ በሁለት አናስ ገዛ:: በደንብ ካጠበውም በኋላ: መልሶ በ4 ወይንም በ 5 አናስ ሸጠው:: እንዲህም በማድረግ በተደጋጋሚ በመሸጥ የህ ሰው በጣም ሃብታም ሰው ሆነ:: የዚህም አንዱ ቤተሰብ: አንዱ የእኛ የመንፈሳዊ ወንድማችን ነበር:: ናንዲ ቤተሰብ:: የናንዲ ቤተሰብ አሁንም ኒሆን: ከ 400 እስከ 500 የሚሆኑ ቤተሰቦችን እየመገቡ ያስተዳድራሉ:: ትልቅ የባለአባት ቤተሰቦች ናቸው:: የቤተሰቦቻቸውም መመሪያም እንዲህ ነው:: አንድ ወንድ ልጅ ወይንም ልጅአገረድ ስትወለድ: 5000 ሩፒ በባንክ ውስጥ ይቀመጥላቸዋል:: በትዳራቸውም ግዜ: ይህ 5000 ሩፒ ከወለዱ ጋራ ሁኖ ይሰጣቸዋል:: ከዚህ ሌላ ግን የጋራ የሆነ ሃብት የላቸውም:: ከቤተሰቡ ጋራ የሚኖረው ሁሉ ደግሞ: ምግብ እና መጠለያ ያገኛል:: ይህን ይመስላል ኑሮአቸው:: ዋነኛው የናንዲ ቤተሰብ መስራች ግን: ንግዱን የጀመረው ከሞተች አይጥ በመነሳት ነው:: ይህም እውነት ነው:: የሰው ልጅ በእራሱ ለመተዳደር ከፈለገ: መተዳደር ይችላል:: በካልካታ ይህንን አይቻለሁ:: በጣም ድሃ የሆኑ ቫይሻዎች እንኳን: በጥወት ተነስተው ዳል (የምስር ዘር) በየቤቱ ያዞሩ ነበር:: የከረጢት ዳል ይዘው በየቤቱ እየዞሩ ይሸጡ ነበር:: ዳል በየቤቱ ያስፈልጋል:: እንዲሁም እያደረጉ: ጥዋት ጥዋት ዳል እየሸጡ: ማታ ማታ ደግሞ የኬሮሲን ዘይት ይዘው በየቤቱ ይሸጣሉ:: ማታ ማታ ይህም ስለሚያስፈልግ ነው:: አሁንም ድረስ በህንድ አገር ይህ እየተካሄደ ነው:: ማንም ለመቀጠር ግድ የለውም:: ያለውን ትንሽ ነገር ሽጦ ያድራል:: ኦቾሎኒም ቢሆን ሌላ ነገር ሽጦ ያድራል:: አንድ ነገር ሰርቶ ያድራል:: ጌታ ክርሽና ለሁሉም መተዳደሪያ ይሰጣል:: ይህ ሰው መተዳደሪያዬን ይሰጠኛል ብሎ ማሰብ ስህተት ነው:: ሻስትራ (ቅዱስ መጽሃፍ) እንዲህ ይላል:: "ኤኮ ባሁናም ቪዳድሃቲ ካማን" ማመን ያለብንም "ጌታ ክርሽና ህይወት ሰጥቶኛል: ወደዚህ አለምም አምጥቶኛል:" ስለዚህም መተዳደርያዬንም ያቀርብልኛል::" "ስለዚህም እንደ አቅሜ የቻልኩትን ላድርግ" "ይሁንእንጂ: ጌታ ክርሽና በዚህ መነሻ: መተዳደርታዬን ያቀርብልኛል::"