AM/Prabhupada 0010 - ክርሽናን ለማስመሰል አትሞክሩ፡፡

The printable version is no longer supported and may have rendering errors. Please update your browser bookmarks and please use the default browser print function instead.


Lecture on SB 7.9.9 -- Mayapur, February 16, 1976

የክርሽና: እነዚህ 16000 ባለቤቶች: እንዴት ባለቤቱ ሊሆን ቻሉ? ታሪኩንም ታውቁታላችሁ: 16000 በጣም የሚያምሩ ነበሩ:: ማለቴም: የነገስታት ልጅአገረዶች ሁሉ: በክፉ ስይጣናዊ ታፍነው ተወስደው ነበር:: የዚህስ ክፉ ሰው ስሙ ማን ነበር? "ብሆማአሱራ" ነበር:: እነዚህም ልእልቶች: ለጌታ ክርሽና "በዚህ መጥፎ ታፍነን ተወስደን በስቃይ ላይ ነው ያለነው እና: እባክህ ከዚህ ፈተና አድነን" ብለው ፀሎት አደረጉ:: ስለዚህም ጌታ ክርሽና: ሊያድናቸው መጣ:: ብሆማሱራም ተገድሎ: ልጅ አገረድ ልዕልቶቹ ሁሉ ነፃ ሊወጡ ቻሉ:: ነጻ ከወጡ በኋላም መንገድ ሳይቀጥሉ: እዚያው ቆመው ቀሩ:: ጌታ ክርሽናም እንዲህ አላቸው: "አሁን ወደ ቤት: ወደ አባታችሁ መሄድ ትችላላችሁ አላቸው::" እነርሱም "አንዴ ታፍነን ተወሰደን ስለነበረ: አሁን ሊያገባን የሚችል የለም" ብለው ተናገሩ:: በህንድ አገር ውሰጥ: አሁንም በአንዳንድ ቤተሰብ: ይህ መመሪያ አለ:: አንድ ልጅ አገረድ: ለአንድ ወይንም ለሁለት ቀን: ከቤትዋ ውጪ ካደረች: የሚያገባት ሰው አይኖም:: የሚያገባት ሰው አይኖም:: ምክንያቱም ተደፍራ ይሆናል ተብሎ ስለሚገመት ነው:: በህንድ አገር ይህ መመሪያ አሁንም አለ:: እነዚህም ልእልቶች ለብዙ ቀን እና ለብዙ አመታት ተይዘው ነበር:: ልእልቶቹም አባቶቻችን እንኳን ሊቀበሉን አይችሉም: ብለው: ለክርሽና አማፀኑት:: ማንም ሰው ሊያገባንም አይስማማም ብለው ተናገሩ:: ክርሽናም ሃሳባቸውን ተረዳላቸው: ያሉበትም ደረጃ: የቀና አለመሆኑንም ተረዳላቸው:: በክርሽና ይፈቱም እንጂ: የሚሄዱበት ግን የላቸውም:: ከዚህም ክርሽና: እንደ ደግነቱ "ብሃክታ ቫትሳላ" እንዲህ ጠየቃቸው "ምን ማድረግ ትፈልጋላችሁ?" እነርሱም እንዲህ አሉ: "አንተ እራስህ ካልተቀበልከን በስተቀር: ሌላ ቦታ የምንሄድበት ቦታ የለንም" ብለው ተናገሩ:: ክርሽናም ወዲያውኑ "እሺ እንሂድ አላቸው" ይህ ጌታ ክርሽና ነው:: እነዚህም 16000 ልእልት ሚስቶቹም በአንድ ካምፕ ውስጥ ታጉረው አልተቀመጡም:: ክርሽና ወዲያውኑ 16500 ቤተ መንግስቶች ገነባ:: ሁሉንም እንደ ሚስቶቹ ስለተቀበላቸውም: እያንዳንዳቸውን እንደሚስት ሊንከባከባቸው ወሰነ:: መሄጃ የላቸውም ብሎም አስቦ ሳይሆን: እንደ ንግስቶች በክብር ሊንከባከባቸው አሰበ:: እንዲሁ ላስጠጋቸው ብሎ ብቻ አላሰበም:: በክብር: እንደ ንግስቶች: እንደ ክርሽና ንግስቶች: ለከባንከባቸው አሰበ:: እንዲህም አሰበ "16000 ንግስቲት ባለቤቶቼ" እኔ ብቻዬን ከሆንኩ ግን እንዴት እያዳንዳቸው ሊያገኙኝ ይችላሉ ብሎም አሰበ:: ብቻዬን ከሆንኩኝ: እያንዳንዳቸው 16000 ቀናት መቆየት ሊኖርባቸው ነው:: ይህንንም በማሰብ ጌታ ክርሽና 16000 ጌዜ እራሱን ለማባዛት ወሰነ:: ይህ ጌታ ክርሽና ነው:: እነዚህ ተንኮለኛ ሰዎች ግን: ክርሽና ሴቶች ጠላፊ ነው ብለው ያሙታል:: ክርሽና እንደኛ አይደለም:: እኛ አንድ ሚስት እንኳን ለማስተዳደር ያዳግተናል:: ጌታ ክርሽና ግን 16000 ሚስቶች ይዞ በ16000 ቤተመንግስት ውስጥ ለማስተዳደር ይችላል:: እራሱንም ለእያንዳንዷ ንግስት አባዝቶ አንድ በአንድ ለማስተዳደር ይችላል:: በዚህም መንገድ እያንዳንዷን ንግስት ለማስደሰት በቃ:: ይህ ጌታ ክርሽና ነው:: የክርሽናን ማንነት በዚህ መንገድ መረዳት እንችላለን:: ክርሽናን ለመምሰል መሞከር የለብንም:: በመጀመሪያ ደረጃ የክርሽናን ማንነት መረዳት አለብን::