AM/Prabhupada 0011 - ክርሽናን በሀሳብ ለማምለክ ይቻላል፡፡

The printable version is no longer supported and may have rendering errors. Please update your browser bookmarks and please use the default browser print function instead.


Lecture on BG 4.28 -- Bombay, April 17, 1974

በ "ብሃክቲ ራሳ አምርታ ሲንዱ" አንድ ታሪክ አለ:: ታሪክ ብቻ ሳይሆንም የእውነት ታሪክ ነው:: እንዲህም ተገልፆ ነበር:: አንድ በጣም ትጉህ: የአምላክ አገልጋይ ብራህመና (ቄስ) ነበረ:: በቤተመቅደስ ውስጥም በጣም ጥሩ የሆነ አገልግሎት ለመስጠት ፈለገ:: ነገር ግን ገንዘብ አልነበረውም:: አንድ ቀንም በ "ብሃገቨድ ጊታ" የቅዱስ መጽሃፍ የትምህርት ሰበካ ክፍል ውስጥ ተቀምጦ ነበር:: በዚህም ትምህርት ላይም እንዳለ: ጌታ ክርሸናን በአእምሮም ለማምለክ እና ለማገልገል እንደሚቻል ተረዳ:: ይህንንም ለረጅም ግዜ ያስብ ስለነበረ: ይህን እድል ለመጠቀም አሰበ:: ጌታ ክርሽናንም በከፍተኛ እና በውድ መንገድ ለማገልገል ተመኘ: ነገር ግን ገንዘብ አለነበረውም:: ጌታ ክርሽናም በአእምሮ እንደሚመለክም ሲሰማ: በቅዱስ ጎዳቨሪ ወንዝ ውስጥ ተጠምቆ: በዛፍ ስር ቁጭ አለ:: ከዚህም ቦታ ሁኖ: በአእምሮው: ውስጥ: በጣም የሚያምር እና ውድ የሆነ "ሲምሃሳና" ዙፋን መገንባት ጀመረ:: ይህንንም ዙፋን በወርቅ እና ጌጣ ጌጥ አሸብርቆ: እና የጌታ ክርሽናን ምስል አስቀምጦ: በአእምሮው የጌታ ክርሽናን ገላ ማጠብ ጀመረ:: የሚጠቀውም ውሃ ከተቀደሱት ወንዞች: ከጋንጀስ: ከጀሙና: ከጎዳቨሪ: ከካቬሪ: በመውሰድ ነበረ:: ከዚያም የጌታ ክርሽናን ገላ በጥሩ ሁኔታ ማልበስ እና በአበባ የተሰሩ ጋርላንዶችን ማቅረብ ጀመረ:: ከዚያም ለጌታ ክርሽና: በጣም ጥሩ የሆነ ምግብ: ማዘጋጀት ጀመረ:: የፓራማና የተባለውን የጣፋጭ ሩዝም ማዘጋጀት ጀመረ:: ይህንንም ጣፋጭ ሩዝ ትኩስ ስለመሆኑ መቅመስ ፈለገ:: መቅመስም የፈለገው: ፓራማና ጣፋጭ ሩዝ: በቀዝቃዛ እንጂ: ትኩስ ሆኖ ስለማይቀርብ ነው:: ለሙከራም ጣቱን ሲነክርበት: ጣቱ ወዲያው ተቃጠለ:: በዚህን ግዜ የአእምሮው ሜዲቴሽን ተደናቀፈ: ምንም ነገር በአጠገቡም እንደሌለ ተረዳ:: ይህን ሁሉ ያደርግ የነበረው በአእምሮው ነበረ:: ነገር ግን: ጣቱ ተቃጥሎ በማግኘቱ በጣም ተደነቀ:: በዚህም ምክንያት: ጌታ ናራያና ከቫይኩንታ: ሁኖ መሳቅ ጀመረ:: ላክሽሚ: (ባለቤቱ) ለምን ትስቃለህም ብላ ጠየቀችው:: አንዱ የእኔ አጋልጋይ እንዲህ አድርጎ በፍቅር አገለገለኝ ብሎም አጫወታት:: ለእርሱ አገልጋዮችም ወደ ቫይኩንታ ይዘውት እንዲመጡም ትእዛዝ ሰጠ:: እንዲሁም ሁሉ "የብሃክቲ ዮጋ" (የጌታ ፍቅር አገልግሎት) በጣም ደስ የሚል ነው:: ጌታን በብዙ ሃብት ለማገልገል አቅም ባይኖረንም: በአእምሮአችን እንኳን አምላክን በፍቅር ማገልገል እንችላለን::