AM/Prabhupada 0012 - የእውቀት ሁሉ መነሻ በማዳመጥ መሆን አለበት፡፡

The printable version is no longer supported and may have rendering errors. Please update your browser bookmarks and please use the default browser print function instead.


Lecture on BG 16.7 -- Hawaii, February 3, 1975

እያንዳንዳችን: በሁሉም ነገር የተሟላ ስልት የለንም:: በአይናችን ከመጠን ያለፈ እንኮራለን:: እንዲህም እንላለን "አምላክን ልታሳየኝ ትችላለህ?" እንላለን: ዐይናችን ምን ያህል አማላክን ለይቶ የማወቅ ችሎታ አለውና ነው: "እስቲ አማላክን አሳየኝ“ የምንለው? ሰው ይህን ለይቶ አያስብም: አማላክንም ለይቶ የማወቅ ችሎታም የለውም: ቢሆንም ግን: “አምላክን አሳየኝ” ብሎ ይጠይቃል: እነዚህ ዐይኖቻችን:ለማየት ብዙ ነገር ማስተካከል ያስፈልጋቸዋል: አሁን መብራት ስለ አለ ለማየት ትችላላችሁ: መብራት ከጠፋ ግን: ምንም ነገር ማየት አትችሉም: ታድያ እንደዚህ አይነቱ ዐይን ፍፁምነቱ ምን ላይ ነው? ከዚህ ግድግዳ ጀርባ እንኳን የሚደረገውን ለማየት ያዳግተናል: ስለዚህም በተፈጥሮ ያለንን የስሜት የሰውነት ክፍሎች:ፍፁም ለሆነ እውቀት መነሾ ይሆናሉ ብለን መተማመን የለብንም: የእውቀት መነሾ ከማዳመጥ መሆን አለበት:ይህም “ሽሩቲ” ይባላል: በዚህም ምክንያት: የቬዳዎች ስም:“ሽሩቲ:ሽሩቲ ፕራማና" ይባላል: ልክ ልጅ አባቱን ለማወቅ እንደሚጥር ሁሉ: ይህስ ልጅ እንዴት ነው ስለ አባቱ ለማወቅ የሚችለው?መረጃውም ከ ”ሽሩቲ“ ነው:ይህም ከእናቱ ስለ አባቱ ማንነት በማዳመጥ ነው: እናት: ”ይህ አባትህ ነው“ ማለት ትችላለች: እንደዚህም ሁሉ በማዳመጥ: ይረዳል እንጂ: አባቱ እንዴት ሊሆ ን እንደቻለ ለማየት አይችልም: ልጁ ከመወለዱ በፊት አባቱ በህይወት ስለነበረ: ልጁ አባቱ እንዴት እንደተፈጠረ ሊረዳ አይችልም: እንደዚሁም ሁሉ: በማየት ብቻ:ፍፁም የሆነ እውነትን ለማረጋገጥ አይቻልም: ከባለ ስልጣን መስማት አለብን:እናት ባለ ስልጣን ናት: ስለዚህም ”ሽሩቲ ፕራማና“ መረጃችን ማዳመጥ ነው እንጂ ማየት አይደለም: እነዚህ ፍፁም ያልሆኑ አይኖቻችን:ለማየት ብዙ እንቅፋቶች አሏቸው: እንደዚሁም ሁሉ:በቀጥታ በማየት:ትክክለኛ እውነትን ሁልግዜ ለማግኘት አንችለም: ቀጥታ ማየት ግምት ሊሆን ይችላል:ልክ እንደ ”ዶክተር እንቁራሪት“ ታሪክ ማለት ነው: ”ዶክተር እንቁራሪት“ ስለ አትላንቲክ ውቅያኖስ ግምት ውስጥ ገባ: 3 ሜትር ኩሬ ውስጥ ተቀምጦ: ጓደኛው እንዲህ አለው: ”እኔ ትልቅ ውቅያኖስን አይቻለሁ” አለው: ይህ ውቅያኖስ ማን ይባላል ብሎ ዶክተር እንቁራሪት ጠየቀ:ጓደኛውም “አትላንቲክ ይባላል” ብሎ ነገረው: ምን ያህል ትልቅ ቢሆን ነው ብሎ ጠየቀ: ዶክተር እንቁራሪትም “ምንአልባት አራት ሜትር ይሆን” ብሎ ያስባል: ”ይህ ትልቁ ውቅያኖስ የምትለው: ምናልባት 3 ሜትር ወይንም 4 ሜትር ወይንም 5 ሜትር ስፋት ያለው ሊሆን ይችላል“ብሎ ተናገረ: በል እንጂ ተናገር: ማናልባት 10 ሜትር ስፋት? እና በእንደዚህ በመሰለ ግምት:አትላንቲክ እና ፓሲፊክ ውቅያኖስን እንዴት አድርጎ ዶክተር እንቁራሪት ሊረዳ ይችላል? የአትላንቲክ እና የፓስፊክ ውቅያኖስን ስፋት በግምት ለማወቅ ትችላላችሁን? እንደዚሁም ሁሉ በግምት ትክክለኛ እውቀት ማግኘት አይቻልም: ሳይንቲስቶች ይኅ ህዋ ምን ያህል ኮከቦች እንዳሏት ለመረዳት ለብዙ አማታት ይገምቱ ነበር: የህዋስ ስፋቱ ምን ያህል ነው? ስለ ገዛ ምድራችን እንኳን ብዙ የማናውቀው ነገር አለ: ስለመንፈሳዊው አለሙ ይቅርና: ያ ከአቅማችን በላይ ለመረዳት የራቀ ነው: “ፓራስ ታስማት ቱ ብሃቮ ንዮ ቭያክቶ ቭያክታት ሳናታና” (ብ ጊ 8 20) በ ብሃገቫድ ጊታ የቅዱስ መጽሃፍ ውስጥ ሌላ መንፈሳዊ አለም እንዳለ ተገልጿል: ይህ ፍጥረት የምታዩት: በሰማይ የተከበበ: ከዚህ ከምናየው በላይም: አምስት የተደራረቡ ፍጥረታት አሉ: ልክ እንደ ኮኮናት ፍሬ: የተደራረበ ሽፋን በሰማይም ይገኛል: ጠንካራ የሆነ ሽፋን አለ: ከዚህም ውስጥ ውሃ ይገኛል: በዚህም ሽፋን ውስጥ: እና በውጭ በሚገኘው ሽፋን ውስጥ:ሌላ አምስት አይነት ሽፋኖች አሉ:እነዚህም ከሌሎቹ በጣም ትልቅ ሁነው ይገኛሉ: የውሃ ሽፋን አለ:የአየር ሽፋን አለ: የእሳት ሽፋን አለ:እና እነዚሁን ሁሉ ጥሶ ማለፍ ያስፈልጋል: ከዚያም ወደ መንፈሳዊ አለም መድረስ ይቻላል: እነዚህም ህዋዎች: ቁጥራቸው ሊገመት የማይችል ነው:“ኮቲ” “ያስያ ፕራብሃ ፕራብሃቮ ጃጋድ አንዳ ኮቲ” (ብ ሰ 5 40) “ጃጋድ አንዳ” ማለት ህዋ ማለት ነው: “ኮቲ” ማለት: በብዙ ሚሊዮን የሚቆጠሩ:በአንድነት ማለት ነው:ይህም የምድራዊ አለም ነው: ከዚህም ምድራዊ አለም ባሻገር:የመንፈሳዊ አለም ይገኛል: ያም ሰማይ ነው: የሚባለውም “ፕራቭዮማ” ነው: እንደዚህም ሁሉ: በስሜታችን በመረዳት:በጨረቃ እና በፀሃይ ያለውን ገምተን ለመረዳት አንችለም: ይህች ፕላኔት:በዚህ ህዋ ውስጥ የምትገኝ: እንዲሁም: እንዴት ብላችሁ የመንፈሳዊ አለምን በግምት ልትረዱ ትችላላችሁ?ይህ ሞኝነት ነው: ስለዚህም ”ሻስትራ“ (ቅዱስ መጽሐፎች) እንዲህ ትላለች “አቺንትያ ክሀሉ ዬ ብሃቫ ና ታምስ ታርኬና ዮጃዬት” “አቺንትያ” ማለት ሊረዱት የማይቻል: ከስሜታዊ መረጃዎቻችን የራቁ: በክርክር ሊረዱት የማይቻል ስለሆነ:ግምት ውስጥ አትግቡ: ይህም ሞኝነት ነው:በዚህም መንገድ መረዳት አይቻልም: ስለዚህ ወደ መንፈሳዊ አስተማሪያችን መሄድ አለብን: “ታድቪግናናርትሃም ሳ ጉሩም ኤቫብሂቼት ሳሚት ፓኒህ ሽሮትሪያም ብራህማ ኒሽትሃም (ም ዩ 1 2 12) ይህ ነው ስርአተ ጉዞው: