AM/Prabhupada 0014 - የአምላክ ትሁት አገልጋዮች በክብር የገነኑ ናቸው፡፡

Revision as of 06:06, 29 November 2017 by Sahadeva (talk | contribs) (Text replacement - "<!-- END NAVIGATION BAR --> <!-- BEGIN ORIGINAL VANIQUOTES PAGE LINK-->" to "<!-- END NAVIGATION BAR --> <!-- BEGIN ORIGINAL VANIQUOTES PAGE LINK-->")
(diff) ← Older revision | Latest revision (diff) | Newer revision → (diff)


The Nectar of Devotion -- Calcutta, January 30, 1973

ለድቮቲዎች (አገልጋዮች) ክርሽና በእጃቸው መዳፍ ውስጥ ነው:: "አጂታ ጂቶ ፒ አሶ" ክርሽና በማንም ለመሽነፍ ባይችለም: በፈቃዱ ግን: በአገልጋዮቹ ይሸነፋል: ይህ ነው የሱ ፈቃድ: ልክ በፈቃዱ በእናቱ በያሾዳ እንደተሽነፈም ሁሉ: በፈቃዱም በራድሃራኒ እና በጓደኞቹም ይሸነፋል: አንድ ግዜ በጨዋታም ክርሽና ተሸንፎም: ጓደኛውን በተክሻው ተሽክሟል: አንዳንድ ግዜም ንጉስ ቀልደኛ ሰው አጠገቡ ያስቀምጣል: ይህም ቀልደኛ ሰው:ንጉሱን ይቀልድበታል:ንጉሱም በዚህ ቀልድ ደሰታል: ቀልደኛውም አንድ አንድ ግዜ በቤንጋል ውስጥ አንድ ”ጎፓላ ቦን“ ይባል የነበረ ቀልደኛ ነበረ: አንድ ቀንም ንጉሱ እንዲህ ብሎ ጠየቀው: “ጎፓላ” ከአንተና ከአህያ ልዩነታችሁ ምንድን ነው ብሎ ጠየቀው: ቀልደኛውም ወዲያው ከንጉሱ እና ከእርሱ መሃከል ያለውን ርዝመት መለካት ጀመረ: ከዚያም 3 ፊት ይሆናል ጌታዬ ብሎ መለሰለት: ልዩነቱ 3 ፊት ብቻ ነው ይህንንም ሰምተው ሁሉም መሳቅ ጀመሩ:ንጉሱም ይህንን ስድብ ሰምቶ በመሳቅ ተደሰተ: ይህም አንዳንድ ግዜ ያስፈልጋል: ክርሽናም እንዲሁ ነው: ሁሉም በከፍተኛ ደረጃ አማላክን ያወድሳል: ይህም የክርሽና ደረጃ ነው:ታላቁ ጌታ: በቫይኩንታ መንፈሳዊ አለም አማላክን ማወደስ ብቻ ነው የሚታየው: ሌላ ነገር የለም: በቭርንዳቫን ውስጥ ግን: ክርሽና ከአገልጋዮቹ ነቀፌታ ይቀበላል: ሰዎች የቭርንዳቫን ኑሮ እንዴት እንደሆነ አይረዱም: የክርሽና አገልጋዮች በከፍተኛ ደረጃ የሚገኙ ናቸው: ራድሃራኒ አንዳንድ ግዜ ትእዛዝ ትሰጣለች:“ክርሽና ወደ እዚህ እንዳይመጣ:ክርሽና መግባት አይችልም” ክርሽናም ጎፒዎቹን “እባካችሁ እንድገባ ፍቀዱልኝ” ብሎ ይለምናቸዋል: እነርሱም “ትእዛዝ እንድትገባ አልተሰጠንም እና: መግባት አይፈቀድልህም” ብለው ይከለክሉታል: ክርሽናም ይህን አቀራረባቸውን ይወደዋል: