AM/Prabhupada 0018 - የሎተስ እፅዋት በመሰለው የመንፈሳዊ አባት እግር እምነት ማድረግ፡፡

The printable version is no longer supported and may have rendering errors. Please update your browser bookmarks and please use the default browser print function instead.


Lecture on SB 6.1.26-27 -- Philadelphia, July 12, 1975

ፕራብሁፓዳ እንዲህ አለ: "ይህንን ግዜያችንን መፍትሄ ለማግኘት መጠቀም አለብን" መፍትሄ የሚያስፈልገውም: ለዚሁ በተደጋጋሚ: ለሚወለደው እና ለሚሞተው ህይወታችን ነው:: ታድያ ይህ መፍትሄ: ወደ ትክክለኛ መንፈሳዊ አባት (ጉሩ)ሳይሄዱ:እንዴት ለመረዳት ይቻላል? ስለዚህም “ሻስትራ” (ቅዱስ መጽሃፍ)እንዲህ ይላል “ታድ ቪግናናርትሃም” የሕይወታችሁን ዋናውን ችግር ለማወቅ ከፈለጋችሁ እና: የክርሽና ንቃትን በደንብ ለመረዳት ከፈለጋችሁ: ህይወታቹህ እንዴት ዘላለማዊ መሆን እንደሚችል እና እንዴት ወደ የመጣንበት የአማላካችን ቤት ለመመለስ ማወቅ ከፈለጋችሁ: የመንፈሳዊ አባት “ጉሩ” መቅረብ አለባችሁ: ታድያ ማነው ይህ “ጉሩ”?ይህ በቀላሉ እንዲረዱት ተደርጓል: ጉሩ የራሱን ሃሳብ እንዲህ እያለ አይፈጥርም “ይህንን አድርግ:ገንዘበ ስጠኝ እና:ደስተኛ:ትሆናለህ” ይህ ጉሩ አይደለም:ይህ ለይት ያለ ገንዘብ መሰብሰቢያ ጥበብ ነው: ይህ በሻስትራ “ሙድሃ” (ሞኝ)ብሎ ተጠቅሷል:በእንደዚህ አይነት መንገድ ብዙ ሰው በሞኞች ገነት ውስጥ:ተሰብስበው ይገኛሉ: ልክ እንደ አጃሚል: የራሱን ሃሳብ የሚፈጥር ማለት ነው “ይህ የኔ ስራ ነው” ብሎ የራሱን መንፈሳዊ ሃላፊነት የሚወስድ: የህ ሞኝ ሰው ነው: የመንፈሳዊ ተግባራችሁን መረዳት ያለባችሁ ከጉሩ ነው: እንዲህ እያልንም በቀን በቀን እንዘምራለን :“ጉሩ ሙክሃ ፓድማ ቫክያ:ሲቴቴ ኮሪያ አይካ:አራና ኮሪሆ ማኔ አሳአ” እንዲህ ነው ሕይወታችን መመስረት ያለበት:“ጉሩ ሙክሃ ፓድ” ለትክክለኛ ጉሩ አንደበታችሁን ሰጥታችሁ: የተቀበላችሁትን ትእዛዝ ፈጽሙ: ያን ግዜ ሕይወታችሁ የተሟላ ይሆናል:“አራ ና ኮሪሆ ማኔ አሳአ” አንተ ተንኮለኛ የሆንክ ሰው: ሌላ ምንም ነገር አያስፈልግህም: በቀን በቀን ትዘምራለህ:ትርጉሙን ግን ትረዳዋለህን? ወይስ ዝም ብለህ መዘመር ብቻ ነው? ትርጉሙስ ምንድን ነው? ማንስ ያስረዳሃል?ማንም አያውቅምን? አዎ:ትርጉሙ ምንድን ነው? አገልጋይም እንዲህ አለ:”የእኔ ምኞት አእምሮዬ ንጹህ እህዲሆን ነው“ “ይህም ከመንፈሳዊ አስተማሪዬ ከአፉ ከሚወጡት ቃላቶችን በማዳመጥ ነው” ”ከዚህም ሌላ ምንም የምፈልገው ነገር አይኖ ርም“ ፕራብሁፓዳም እንዲህ አለ:”ይህ ትክክል ነው!ትእዛሱም ይህ ነው “ጉሩ ሙክሃ ፓድማ ቫክያ ሲቴቴ ኮሪያ አይካ” “ቺታ” ማለት ህልውና ወይንም ልቦና ማለት ነው “ይህንን ብቻ አደርጋለሁ! አለቀ!” “የእኔ ጉሩ ማሃራጅ እንዲህ ስለአለኝ: እንዲህ አደርጋለሁ” “ሲቴቴ ኮሪያ አይካ አራ ና ኮሪሆ ማነ አሳአ” ይህ የእኔ ትእቢት አይደለም:ይህን ተግባር የምፈጽመው ትእዛዝን በመከተል ነው: ከመንፈሳዊ ወንድሞቼ ትንሽ ለየት ያለ እርምጃ ብታዩብኝም:ይሄ ትእዛዙን ስለተከተልኩ ነው: እኔ አቅም የሌኝም:ነገር ግን የመንፈሳዊ አስተማሪዬን (ጉሩ) ቃላቶች እንደ ሕይወቴ እና ነፍሴ ወስጀዋለሁ: ይህም እውነት ነው:“ጉሩ ሙክሃ ፓድማ ቫክያ:ሲቴቴ ኮሪያ አይካ” ሁሉም ይህን ፈለግ መከተል ያስፈልገዋል:ነገርግን ከትእዛዙ ውጪ መጨመር እና መቀየር ከጀመረ:ወድቀት ያመጣል: ከትእዛዝ ውጪ መጨመር እና መቀየር አያስፈለግም: ጉሩን መቅረብ ያስፈለጋችኋል:ጉሩ ማለት የአምላክ ክርሽና ታማኝ አገልጋይ ማለት ነው: ለማገልገልም የክርሽናን ትእዛዝ ተቀብሎ ይፈጽማል: እንደዚህም ሰው ውጤታማ ደረጃ ይደርሳል: “እኔ ከጉሩዬ በላይ አወቂ ነኝ” ብላችሁ ትእቢት ካደረባችሁ ግን: “እንደ ፈለግሁ በትእዛዙ ላይ መጨመርም መቀየርም እችላለሁ” ብለን ካሰብን:ውድቀት ያመጣብናል: ይህ ብቻ ነው ትርፉ:አሁን መዝሙሩን ቀጥል: አገልጋይ:“ሽሪ ጉሩ ቻራኔ ራቲ:ኤይ ሴ ኡታማ ጋቲ” ፕራብሁፓዳ: “ሽሪ ጉሩ ቻራኔ ራቲ ኤይ ሴ ኡታማ ጋቲ” ትክክለኛ የመንፈሳዊ እርምጃ ማድረግ ከፈለጋችሁ:ወደ ጉሩ እግር በእምነት መጠጋት አለባችሁ:ከዚያስ? አገልጋይ:“ጀ ፕረሳዴ ፑሬ ሳርቫ አሳአ” ፕራብሁፓዳ: “ጀ ፕራሳዴ ፑሬ ሳርቫ አሳአ:ያስያ ፕራሳዳት” የሁሉም ይቫይሽናቫ ትእዛዝ ይህ ነው! ይህንን ካልተከተልንም: ሞኝ ሁነን እንቀራለን!ይህም በ “አጃሚል ኡፓክያና” ተገልጧል: ዛሬ ይህንን ጥቅስ እያነበብን ነው:“ሳ ኤቫም ቫርታማናህ አግናህ” እንደገናም እንዲህ አለ: እንደገና ቭያሳዴቭ እንዲህ አለ: “ይህም ተንኮለኛ ናራያን በተባለው ልጁ ስራ ተመስጦ ነበር” የናራያናን ማንነትም በደንብ አላወቀም: ልጁን ግን በደንብ ያውቃል: ታሞ በሞት ላይ እያለም የልጁን ስም ናራያናንም ደጋግሞ ይጠራ ነበር: “ናራያን እባክህ ወደ እዚህ ቅረብ:እባክህ ወደ እዚህ ቅረብ ይህን ውሰድ” ክርሽናም የእራሱን ስም ናራያናን በመጥራቱ ምህረቱን ሊያሳየው ፈለገ: ጌታ ክርሽና ምህረት አውራጅ ነው: አጃሚል ወደ ናራያን ለመሄድ ፈልጎ አልነበረም ናራያናን ይጠራ የነበረው: ልጁን በጣም ስለሚወደውም ነው ይጠራው የነበረው: በዚህ አጋጣሚግን:የክርሽናን ቅዱስ ስም “ናራያን”ን ለመጥራት በቃ: ይህም የአጃሚል ጥሩ እድል ሆነ:በዚህም ምክንያት በመንፈሳዊ አለም ስማችንን ወደ መንፈሳዊ ስም እንቀይረዋለን: ለምን?እያንዳንዱ ስማችን የጌታ ክርሽና አገልጋይ መሆናችንን የሚያንፀባርቅ መሆን አለበት: ልክ “ኡፔንድራ” እንደማለት: ኡፔንድራ ማለት ቫማናዴቭ ማለት ነው: እንዲሁም ሁሉ “ኡፔንድራ ኡፔንድራ” ብላችሁ ብትጣሩ:ይህ የመንፈሳዊ ስም ጥሩ በረከትን ያመጣላችኋል: ይህም ወደ በኋላ ተተንትኖ ይገለጽላችኋል: