AM/Prabhupada 0023 - ከመሞታችሁ በፊት በክርሽና ንቃታችሁን አዳብሩ፡፡

The printable version is no longer supported and may have rendering errors. Please update your browser bookmarks and please use the default browser print function instead.


Sri Isopanisad Invocation Lecture -- Los Angeles, April 28, 1970

እዚህ እንደዚህ ተጽፏል: "ይህ ህዋ የራሱ ግዜ (እድሜ) አለው: ይህም የተወሰነው በሰማያት ጌታ ሃይል ነው" ህዋእ እራሱ እንደ ግዙፍ ገላ ይቆጠራል: ልክ እንደ ገላችን: ሁሉም ነገር እንደ አካባቢው ይወስነዋል: ዘመናዊው ሳይንስ የሬላቲቪቲ ህግ አለው: አተም ወይንም ትንሽ ጉንዳን እንደ ፍጥረቱ እድሜ አለው: እኛም እንደ ፍጥረታችን የተወሰነ እድሜ አለን:: እንደዚሁም ሁሉ ይህ ህዋእ (ዩኒቨርስ) ለብዙ ሚሊዮን አመት ይኑር እንጂ: ለዘልአለም የሚኖር ዩኒቨርስ አይደለም: ይህም የተረጋገጠ ነው:: በጣም ግዙፍ ስለሆነ ግን ለብዙ ሚሊዮን አመት ለመኖር ይችላል:: ቢሆንም ግን መጨረሻ ይኖረዋል:: ይህ የፍጥረት ህግ ነው:: እንደዚሁም ሁሉ ግዜው ሲደርስ: ይህ ጊዜያዊ አለማችን የሚፈራርስበት ግዜ ይመጣል:: ይህም የሚከናወነው ሙሉ ሃይል በአለው ጌታ ፈጣሪያችን ነው:: የኑሮ የተተመነልን ግዜ ሲያከትም: በገላችን ውስጥ መቆየት አንችልም: ይህንንም ማንም ሊያዘገየው ወይንም ሊያቆመው አይችልም:: ይህም አስተዳደር ሃይል ያለው ነውና: መቆየት እፈልጋለሁ ብሎ መጣር አይቻልም:: እኔ ህንድ አገር እያለሁም: ይህ ሁኔታ ተፈጥሮ ነበር:: አንድ የምናውቀው በጣም ሀብታም የሆነ ጓደኛችን: ከሞት አፋፍ ላይ ነበር:: ዶክተሩንም እንዲህ ብሎ ጠየቀው: "የአራት አመት እንኳን ህይወት አትሰጠንኝምን?" "አንድ ገና ያልጨረስኩት ፕላን አለኝ" አያችሁን? "አሻ ፓሻ ሳቴይር ባድሃህ" ይህ ሴይጣናዊ አስተሳሰብ ነው:: ሁላችንም እንዲህ እያልን እናስባለን: "ይህን መስራት አለብኝ: ይህን መስራት አለብኝ" ይህ አይቻልም: ዶክተሮቹም ሆኑ አባቶች ወይንም ሳይንቲስቶቹም ቢሆኑ: ማንም ሊያቆመው የማይችለው ነው:: አይሆንም:: አራት አመተ ይቅርና: ግዜው ሲደርስ አራት ደቂቃ እንኳን አይፈቀድም:: ጊዜው እንደደረሰ: ወዲያው መሄድ ብቻ ነው:: ይህ ነው የተፈጥሮ ህግ:: ታድያ ይህ ግዜ ሳይመጣ: ሁላችንም የክርሽናን ንቃት በደንብ መከታተል አለብን:: "ቱርናም ያቴታ" ቱርናም ማለት: በጣም በፍጥነት ማለት ነው:: እንደዚህም ሁሉ በፍጥነት የክርሽናን ንቃት መከታተል አለብን:: "አኑ" ሞት ከመምጣቱ በፊትም ይህንን ስራ እና አገልግሎት በግዜ ማከናወን አለብን:: ይህ አዋቂነት ነው:: አለበለዛ ግን መሸነፍ ነው:: አመሰግናለሁ::