AM/Prabhupada 0024 - ክርሽና በጣም ሩህሩህ ነው፡፡

Revision as of 06:06, 29 November 2017 by Sahadeva (talk | contribs) (Text replacement - "<!-- END NAVIGATION BAR --> <!-- BEGIN ORIGINAL VANIQUOTES PAGE LINK-->" to "<!-- END NAVIGATION BAR --> <!-- BEGIN ORIGINAL VANIQUOTES PAGE LINK-->")
(diff) ← Older revision | Latest revision (diff) | Newer revision → (diff)


Lecture on SB 3.25.26 -- Bombay, November 26, 1974

አርጁና ክርሽናን ፊት ለፊት እያየው: ክርሽና ብሃገቫድ ጊታን አስተማረ:: ይህ ክርሽናን መመልከት እና: ብሃገቫድ ጊታን ማንበብ:አንድ የሆነ ነገር ነው: ምንም ልዩነት የለውም:አንዳንዶችም “አርጁና በጣም እድለኛ ነው” ይላሉ: ይህም ክርሽናን ፊት ለፊት እያየ:ትእዛዝ ስለተቀበለ ነው:ነገር ግን ይህ ትክክለኛ አስተያየት አይደለም: የሚያይ መንፈሳዊ የፍቅር አይን እስከአለን ድረስ: ክርሽና ወዲያው ሊታየን ይችላል: ስለዚህም እንዲህ ተጽፏል:“ፕሬማንጀና ቹሪታ” ፕሬማ እና ብሃክቲ: አንድ ናቸው: “ፕሬማንጃና ቹሪታ ብሃክቲ ቪሎቻኔና ሳንታህ ሳዳይቫ ህርዳዬሹ ቪሎካያንቲ” (ብ ሰ 5 38) ከዚህ ጋራም የተያያዘ አንድ ታሪክ ልነግራችሁ እችላለሁ:በደቡብም ህንድ አገር አንድ ብራህማና ነበር:(ቄስ) “ራንጋናት" የሚባል ቤተ መቅደስ ውስጥም የብሃጋቫድ ጊታን ቅዱስ መጽሃፍ ያነብ ነበር: ቢሃንም ግን የሳንስክሪት ቋንቋም ሆነ ደብዳቤ እንኳን ለማንበብ የማይችል ሰው ነበር: በጎረቤትም ያለ ሰው ሁሉ ይህንን ያውቁ ነበር: እንዲህም አሰቡ :“ይህ ሰው ማንበብ አይችልም:ነገር ግን ብሃጋቫድ ጊታ እያነበበ ይመስላል“ መፅሃፉንም እየገለጠው ነው:”አሃ አሃ“ ከዚያም አንዱ እየቀለደ ጠየቀው ”ብራህመና ሆይ:እንዴት ነው ብሃጋቫድ ጊታ የምታነበው?” እርሱም የሰውየውን አቀራረብ ተረዳ “ይህ ሰው ማንበብ የማላውቅ በመሆኔ ነው የሚቀልደው” ብሎ አሰበ: በዚህም ግዜ ጌታ ቼይታንያ በዚሁ በራንገናት ቤተ መቅደስ ውስጥ ነበረ: ጌታ ቼታንያም ይህ ሰው “የክርሽና አገልጋይ” መሆኑን ተረዳ: ስለዚህም ጠጋ ብሎ እንዲህ ጠየቀው “ውድ ብራህማና: ምን እያነበብክ ነው ያለኀው?“ ብራህመናውም ይህ ሰው እንደማይቀልድበት ተረዳ: እንዲህም አለ:”የኔ ጌታ:የማነበው ብሃጋቫድ ጊታ ነው:ለማንበብም እየሞከርኩ ነው:ነገር ግን ማንበብ አልችልም“ ብሎ ተናገረ: የኔ ጉሩ (የመንፈሳዊ አስተማሪዬ)እንዲህ አለኝ:”በቀን በቀን 18 ምእራፎች ማንበብ አለብህ“ ብሎ አዞኛል: እኔ ግን ምንም እውቀት የለኝም:ማንበብም አልችልም: ቢሆንም ጉሩ ማሃራጅ አዞኛል:ስለዚህ እኔም ትእዛዙን ለመከተል እየሞከርኩኝ ነው: እና ገፆቹን ብቻ ነው የምገልጠው እንጂ ለማንበብ አልችልም:ብሎ ተናገረ: ጌታ ቼይታንያም ”ስታነብ አንዳንድ ግዜ ስታለቅስ አይሃለሁ“ አለው: እርሱም ”አዎ አንዳንድ ግዜም አለቅሳለሁ“ አለ: ”ታድያ ማንበብ የማትችል ከሆነ: እንዴት ለማልቀስ ቻልክ“ ብሎ ጠየቀው: ”የብሃጋቫድ ጊታ መጽሀፉን ሳነብ:አንድ ስእል አያለሁ“ ”በዚህም ስእል ክርሽና በፍቃዱ የጋሪ ነጂ ሁኖ ይታያል:”የአርጁና ሳረቲ“ ወይንም ጋሪ ነጂ: “አርጁና የክርሽና አገልጋይ ቢሆንም:እዚህ ላይ ክርሽና በፍቃዱ የአርጁና አገልጋር ሁኖ ይታያል” ”አርጁናም ትእዛዝ ሲሰጥ እና: ክርሽናም ሲያገለግለው ይታያል:“ “ክርሽና በጣም ሩህሩህ ነው:ይህንንም ስእል በሃሳቤ ቀርጬ ሳየው:ለቅሶ እና እንባዬ ይመጣብኛል” ጌታ ቼይታንያም ወዲያውኑ አቀፈው:ከዚያም ”አንተ ብሃጋቫድ ጊታን እያነበብክ ነው“ አለው: “ያለ ምንም ትምህርት ብሃጋቫድ ጊታን እያነበብክ ነው ያለኅው” ከዚያም እቅፍ አደረገው:እንዴትም በጥሞና ስእሉን ይመለከት እንደነበረ ተረዱ: የክርሽናም ፍቅር ስለነበረው: ጥቅሶቹን ቢያነብም ባያነብም ምንም ለውጥ አያመጣም ነበረ: ልቦናው በክርሽና ፍቅር ተመስጦ ነበረ:እንዲሁም ተመስጦ ይመለከት ነበረ: ክርሽና ተቀምጦ:የአርጁናን ጋሪ ይነዳ ነበረ: