AM/Prabhupada 0027 - ከዚህ ሕይወት ባሻገር ሌላ ሕይወት እንዳለ አያውቁም፡፡

Revision as of 06:06, 29 November 2017 by Sahadeva (talk | contribs) (Text replacement - "<!-- END NAVIGATION BAR --> <!-- BEGIN ORIGINAL VANIQUOTES PAGE LINK-->" to "<!-- END NAVIGATION BAR --> <!-- BEGIN ORIGINAL VANIQUOTES PAGE LINK-->")
(diff) ← Older revision | Latest revision (diff) | Newer revision → (diff)


Lecture on CC Adi-lila 7.1 -- Atlanta, March 1, 1975

የመጽሃፍ ንባብ: "በዚህ አለም በተወሰነ አይነት ኑሮ የሚኖር ሰው ሁሉ: እርዳታ የሌለው ሁኔታ ላይ ሁኖ ይገኛል" ነገር ግን ይህ ውስን ላይ ያለ ነፍስ ሁሉ: በማያ ምትሃት ወይንም በአማላክ የውጪያዊ ሃይል አማካኝነት እንዲህ ብሎ ያስባል: "እኔ በአገሬ: በህብረተ ሰቤ: በጓደኞቼ እና በፍቅር ተደግፌአለሁ:" ነገር ግን ሞት ስትመጣ ማንም ሊደግፈው እንደሚችል አይገነዘብም: ይህ ምትሃት ወይንም ማያ ይባላል: ነገር ግን ይህንን አያምንም:: በማያ ምትሃትም: ምን ሊያድነው እንደሚችልም ሊረዳ ወይንም ሊያምን አይችልም:: መዳን ማለት እራስን ከዚህ ከተደጋጋሚ መወለድ እና መሞትን ማዳን ማለት ነው:: ይህ ነው መዳን ማለት:: እንሱ ግን ይህንን አይረዱም:: ንባብ: "የተፈጥሮ ህግጋት ሃይለኛ ከመሆናቸው የተነሳ: የትኛውም አለማዊ ሃብታችን: ከዚህ ከክፉ ሞት ሊያድነን አይችልም:: ሁሉም ሰው ይህን ያውቃል:: ይህ ነው ትልቁ ችግራችን:: ማነው ሞትን የማይፈራው? ሁሉም ሞትን ይፈራል:: ለምን? ምክንያቱም ነፍስ ሟች ስለአልሆነች ነው:: ነፍስ ዘለአለማዊ ናት:: ስለዚህም ትውልድ: ሞት: እርጅና: እና ህመም እነዚህ ሁሉ ነገሮች ሁሉ: ለነፍስ አሸባሪዎች ናቸው:: ምክንያቱም ነፍስ ዘላለማዊ ናት:: ነፍስ አትወለድም:: "ና ጃያቴ" ነፍስ ስለማትወለድ: መሞትም አትችልም:: "ና ምርያቴ ካዳቺት" ይህ ነው የነፍሳችን ትክክለኛ ደረጃ" ስለዚህም ሞትን እንፈራለን:: ይህ ነው የተፈጥሮአዊ ዝንባሌያችን:: እና ከሞት ለመዳን ሁሌ እንጥራለን:: ይህ የሰው ልጅ የመጀመሪያ ጥረቱ ነው:: ይህንንም የክርሽና ንቃተ ትምህርት የምናስተምረው: የኑሮን አላማ ለማስተማር ነው:: ይህ የሁሉም ሰው አላማ መሆን አለበት:: ይህም የቅዱስ መጽሃፍቶች ህግጋት ነው:: እነዚህ የሚንከባከቡን ሁሉ: መንግስት: አባት: አስተማሪ: የልጆች ተንከባካቢዎች ናቸው:: የአለምን ህዝብ እንዴት እንክብካቤ መስጠት እንዳለብንም ማወቅ አለባቸው:: "ና ሞቻዬድ ያህ ሳሙፔታ ምርትዩም" እና ይህ ፍልስፍና በአለም ላይ የት አለ? ይህ ፍልስፍና በአለም ላይ አይታይም:: ይህ የክርሽና ንቃተ ማህበራችን: ይህንን ፍልስፍና እያስተማረ ይገኛል:: እንዲሁም በግምት ሳይሆንም: ስልጣን ያለውን የቬዲክ ቅዱስ ጽህፈቶችን ተመርኩዞ ነው:: ይህ ነው የእኛ ትእዛዝ: በተለያየ ቦታም የምድር ሰውን ለማገልገል ቅርንጯፎች ከፍተናል:: ይህም የህይወትን አላማ የሰው ልጅ ስለዘነጋ ነው:: ከሞትም በኋላ ህይወት እንዳለ የሰው ልጅ ስለዘነጋ ነው:: ይህንን ሁሉ የሰው ልጅ ዘንግቷል:: ያለ ምንም ጥርጣሬ: ከሞት በኋላ ህይወት አለ: ከሞት በኋላ ላለውም ህይወት በዚህ ኑሮ አችን መዘጋጀት እንችላለን:: ወደ ከፍተኛም ፕላኔቶች ሂዶ ከዚህ ምድር የበለጠ ምቾት ያለው ህይወት ለማግኘት መዘጋጀት ይቻላል:: እዚህም የተረጋገጠ ኑሮ መያዝ ይቻላል:: እዚህ የተረጋገጠ ማለቴም አለማዊ ህይወት ከተፈለገ ማለት ነው:: እንዲህም ተብሏል: "ያንቲ ደቫ ቭርታ ዴቫን ፒትርን ያንቲ ፒትር ቭራታሃ ብሁታኒ ያንቲ ብሁቴያ ማድ ያጂኖ ፒ ያንቲ ማም (ብጊ 9 25) እንዲሁም ሁሉ ወደ አለማዊ ገነት ውስጥ ለመግባት: በዚህ አለም ላይ መዘጋጀት ትችላላችሁ:: ወይንም እዚህ አለም ላይ በተሻለ ህብረተሰብ ውስጥ ለመወለድ መዘጋጀትም ትችላላችሁ:: ወይንም ጎስቶች ያሉበት እና የሚቆጣመሩበት ፕላኔትም ለመሄድ ይቻላል:: ወይንም ደግሞ ጌታችን ክርሽና ወደ አለበት ፕላኔትም መሄድ ይቻላል:: ሁሉም ነገር ለሰው ልጅ ክፍት ነው:: "ያንቲ ብሁቴጅያ ብሁታኒ ማድ ያጂኖ ፒ ያንቲ ማም" እራሳችሁን ማዘጋገት ብቻ ነው የሚገባችሁ:: ልክ በወጣት ግዜያችሁ ትምህርት ትማራላችሁ:: ከዚያም አንዱ ኤንጂንዬር ሊሆን ይችላል:: ሌላው የመድሃኒት ትምህርት ተምሮ ይመረቅ ይሆናል:: ሌላው የህግ ምሩቅ ሊሆን ይችላል:: እዲሁም ብዙ ባለሙያዎች ይመረቃሉ:: ለዚህ ሁሉ የሚዘጋጁትም በትምህርት ነው:: እንደዚህም ሁሉ ለወደፊት ትውልዳችሁ አሁን መዘጋጀት ትችላላችሁ:: ይህ ለመረዳት አስቸጋሪ አይደለም:: ሰዎች ከሞት በኋላም ህይወት እንዳለም አያምኑም:: ምንም እንኳን ለመረዳት ቀላል ቢሆንም:: ከሞት በኋላም ህይወት እንዳለ የምንረዳው ክርሽና ስለ ነገረን ነው:: በትንሽም እውቀት ይህን ፍልስፍና: ሌላ ህይወት እንደሚኖረን እንረዳለን:: ስለዚህ የእኛ አሰተያየት: "ለሚቀጥለው ህይወታችሁ አሁን የምትዘጋጁ ከሆነ: ለምን ወደ መጣንበት የአማላካችን ቤት ተመልሰን ለመሄድ ጥረት አናደርግም? ይህ ነው የእኛ አሰተያየት::