AM/Prabhupada 0028 - ቡድሀ አብዩ አምላክ ነው፡፡

Revision as of 06:07, 29 November 2017 by Sahadeva (talk | contribs) (Text replacement - "<!-- END NAVIGATION BAR --> <!-- BEGIN ORIGINAL VANIQUOTES PAGE LINK-->" to "<!-- END NAVIGATION BAR --> <!-- BEGIN ORIGINAL VANIQUOTES PAGE LINK-->")
(diff) ← Older revision | Latest revision (diff) | Newer revision → (diff)


Lecture on Sri Isopanisad, Mantra 1 -- Los Angeles, May 3, 1970

ጋርጋ ሙኒ (ንባብ): "ቨጂቴርያን (አትክትልት ብቻ የሚበላ ሰው) በመሆንም ብቻ" "ከተፈጥር ህግጋት በላይ መሆን እንችላለን ማሰብ ትክክል አይደለም" አትክልቶችም ህይወት አላቸው:: በተፈጥሮ ህግ: አንዱ ህይወት በሌላው ህይወት ላይ ነው ተመግቦ የሚኖረው:፡ ገና ለገና ቨጅተሪያን ነን ብለን ትእቢት እንዲሰማን አያስፈልግም:: ዋናው ነጥብ አማላክን ለመረዳት ማቻል ነው:: እንስሶች አማላክን የመረዳት ስጦታ የላቸውም: የሰው ልጅ ግን ይህ ስጦታ አለው:: ፕራብሁፓዳ: ይህ ነው ዋናው ነጥብ መረዳት የሚኖርብን:: ቡዲስቶችም ቨጅቴሪያን ሁነው እናገኛቸዋለን:: ከቡዲስቶችም መመሪያ አንፃር ስናየው: አሁን አሁን ሁሉም ነገር እየረከሰ መጥቷል: ነገር ግን ጌታ ቡድሃ ለማስተማር የመጣበት አላማ: እነዚህ ተንኮለኞች እንስሳዎችን መግደል እንዲያቆሙ ነበር:: "አሂምሳ ፓራሞ ድሃርማ" የጌታ ቡድሃ ወደ እዚህ አለም ላይ ስለመምጣት በሽሪማድ ብሃጋቫታም እና በብዙ ቬዲክ መጻህፍቶች ውስጥ ተገልጿል:: "ሹራ ድቪሻም" የመጣበትም አላማ ሰይጣናዊ አቀራረብ ያላቸውን ለማታለል ነው:: "ሰይጣኖች" እነዚህንም ለማታለል ጥሩ መመሪያ ፈጥሮ ነበር:: እንዴትስ ሊያታልላቸው በቃ? ሰይጣኖች ማለት አማላክን ተቃዋሚዎች ማለት ነው:: በአማላክ አያምኑም:: ጌታ ቡድሃም እንዲህ ብሎ አስተማረ: "በእርግጥ አማላክ የለም ነገር ግን እኔ የምላችሁን ተከተሉ" "እሺ ጌታዬ" ብለውም ተቀበሉ:: እራሱ ግን አምላክ ነበረ:: እንዲህ አድርጎም አታለላቸው:: እነዚህም ሰዎች በአማላክ አያምኑም ነበር: ነገር ግን በቡድሃ ያምኑ ነበር: ቡድሃ ደግሞ እራሱ አምላክ ነበር:: "ኬሻቫ ድህርታ ቡድሃ ሻሪራ ጃያ ጃጋድ ኢሻ ሀሬ" ስለዚህ የሰይጣን እና የአማላክ አገልጋይ ልዩነታቸው ይህ ነው:: የክርሽና አገልጋይ እነዚህ ተንኮለኞችን እንዴት ክርሽና ኬሻቫ እንዳታለላቸው ይረዳል: አገልጋይ ይህንን በደንብ ይረዳል: እነዚህ የሰይጣን መንፈስ ያላቸው ደግሞ “ጥሩ መሪ አለን ብለው ያስባሉ” መሪያችንም በአማላክ አያምንም ብለው ያስባሉ: “ሳቅ” አያችሁን? “ሳሞ ሃያ ሱራ ድቪሻም (ሽብ 1 3 24 )የዚህ ትክክለኛ ጥቅስም በሳንስክሪት ቋንቋ ተመዝግቧል: ይህንንም አይታችኋል:እንዲህም ታነባላችሁ:”ሳሞሃያ“ ለማዋከብ ”ሱራ ድቪሻም“ ”ሱራ ድቪሻም“ ማለት የአማላክ አገልጋይ ምቀኞች ማለት ነው: በአማላክ የማያምኑ ሁሉ:ሁልግዜ በአማላክ አገልጋዮች እንደተመቀኙ ነው: ይህም የተፈጥሮ ህግ ነው: ይህም በአባት አይተነዋል:”አባት ለ5 አመት ልጁ ጠላት ሁኖ ነበር“ የልጁ ስህተት ምንድን ነበር?ልጁም የአምላክ አገልጋይ ነበር: ልጁም በጣም ጨዋ ነበር:ፍላጎቱም ሁሉ የአምላክን ስም “ሃሬ ክርሽናን ማንትራ” ለመዘመር ብቻ ነበር: አባቱ ግን የልጁ ሃይለኛ ጠላት ሁኖ ተገኘ:“ልጁንም ግደሉት ብሎ ትእዛዝ ሰጠ” እና አባት እንደዚህ ጠላት ሁኖ የሚገኝ ከሆነ:ሌሎቹስ ሰይጣኖች እንዴት ሁነው ይገኛሉ? እና:የአማላክ አገልጋይ መሆን ስትጀምሩ በአለም ላይ ብዙ ጠላቶች እንደምታፈሩ መረዳት አለባችሁ: ነገር ግን የአማላክ አገልጋዮች ናችሁና ይህን መታገል ሃላፊነታችሁ ነው: ሚሽናችሁም እነሱ እንዲረዱ እና እንዲበለጽጉ ነው: ልክ እንደ ጌታ ኒትያናንዳ: ሲያስተምር ሰይጣኖች ጎድተውት ነበረ: ቢሆንም ግን የጎዱትን ጃጋይ እና ማድሃይ ከሃጥያት ነፃ ሊያወጣቸው በቃ: ይህ ነው መመሪያችን ሊሆን የሚገባው: አንዳንድ ግዜ ማታለል ወይንም መጎዳት ሊያስፈልገን ይችል ይሆናል: ዋናው አላማ ግን እንዴት የሰው ልጅ የክርሽና ንቃቱን ለማዳበር እንደሚችል መጣሩ ነው: ይህ ነው የእኛ ሚሽን ወይንም አላማ: እንደምንም ብለን እነዚህ ተንኮለኞች እንዴት የክርሽናን ንቃት እንደሚከተሉ ለማድረግ ነው ጥረታችን: