AM/Prabhupada 0029 - ቡድሀ ከሀድያንን አታለላቸው፡፡

Revision as of 06:06, 29 November 2017 by Sahadeva (talk | contribs) (Text replacement - "<!-- END NAVIGATION BAR --> <!-- BEGIN ORIGINAL VANIQUOTES PAGE LINK-->" to "<!-- END NAVIGATION BAR --> <!-- BEGIN ORIGINAL VANIQUOTES PAGE LINK-->")
(diff) ← Older revision | Latest revision (diff) | Newer revision → (diff)


Sri Isopanisad, Mantra 1 -- Los Angeles, May 3, 1970

ጌታ ቡድሃ ሰይጣናሞቹን ሁሉ አታለላቸው: ለምንድን ነው ግን ያታለላቸው?“ሳዳያ ህርዳያ ዳርሺታ ፓሹ ግሃታም” እርሱም በጣም ለሌሎች የሚያዝን ስለነበረ ነው: አምላክ ሁልግዜ ለስነፍጥረቶች ሁሉ ያዝናል:ምክንያቱም ሁሉም ልጆቹ ስለሆኑ ነው: እነዚህም ተንኮለኞች ምንም ገደብ በሌለው መንገድ እንስሶችን በመግደል ላይ ይገኙ ነበር: ለምን ትገላላችሁ ብላችሁ ብትጠይቋቸው ደግሞ ወዲያውኑ በቬዳ ውስጥ ለመግደል ተፈቅዷል ብለው ይመልሳሉ:“ፓሻቮ ቫድሃያ ስርስታ” እንስሳ መግደል በቬዳ ውስጥ በእርግጥ ተጠቅሷል: ነገር ግን አላማው ምንድን ነው? ይህም አላማ የቬዲክን ማንትራ (የፀሎት ቃላቶች) ለመሞከር ነበር: እንስሳው በእሳት ውስጥ ከተቀመጠ በኋላ: በቬዲክ ማንትራ ህይወት እንዲሰጠው ይደረግ ነበር: ይህም ለመስዋእት የሚቀርበው ለዚህ አላማ ነው እንጂ ገድሎ ለመብላት አልነበረም: ስለዚህም በዚህ “ካሊ” በተባለው ዘመናችን ውስጥ: ጌታ ቼይታንያ ይህ እንዳይደረግ ከልክሏል: ምክንያቱም በአሁኑ ግዜ ይህንን የእንስሳን መስዋእት በደንብ አድሮጎ የሚያከናውን ብራህመና አይገኝም: ይህም የቬዲክ ማንትራውን ለመለማመድ ማለት ነው: ያግያ (መስዋእቱን) ከማከናወናቸው በፊት ማንትራው ምን ያህል ሃይል እንዳለ ለማየት ፕላን ያደርጋሉ: ይህም የሚሞከረው እንስሶችን በመሰዋት ነው:ከዚያም ለእንሰሶቹ ህይወት ይሰጥዋቸው ነበር: ህይወትም ከአገኙም በኋላ ቄሶቹ ማንትራው በደንብ እንደሰራላቸው ይረዱ ነበር: ይህም መስዋእት ይህን ማንትራ ለመሞከር ነው እንጂ:እንስሳውን ገድሎ ለመብላት አልነበረም: እነዚህ ተንኮለኞች ግን:እንሰሳ ገድሎ ለመብላት ብለው “በቬዳ ውስጥ እንስሳ መግደል ተፈቅዷል” ብለው ይናገራሉ: ልክ እንደ ካልካታ:ካልካታ ሂዳችሁ ነበር? አንድ ኮሌጅ መንገድ የሚባል ነበረ:አሁን ስሙን ቀርረውታል: አሁን “ቪድሃን ራያ” ሳይሉት አይቀሩም: እዚያም እንስሳ ማረጃ ቦታ ይገኛል: ህንዶቹም ከዚህ እንስሳ ማረጃ ቦታ አይገበዩም: ስጋ ከእስላም ስጋ መሸጯ ቦታ ሂደው አይገዙም: ያም ንጹህ ስለአልሆነ ነው:ብለው ያስባሉ ነገር ግን ያም ይህም ሰገራ ያው ነው ሁለቱም ስጋ እየበሉ የሂንዱ ንጹህ እና የእስላሙ ንጹህ ያልሆነ ብለው ያስባሉ ይህ የጭንቅላታቸው ግምታዊ ሃሳብ ነው: በሃይማኖት ስም ይህ እየተካሄደ ነው: በዚህም ምክንያት:እኔ ሂንዱ: እኔ እስላም: እኔ ክርስቲያን እያሉ ይጣላሉ: ማንም ሰው ሃይማኖትን በትክክል የሚረዳ አይመስልም: እነዚህ ተንኮለኞች ሃይማኖትን ትተዋል: ሀይማኖታቸው ጠፍቷል: የክርሽና ንቃት አማላክን እንዴት እንደምንወድ ያስተምረናል:ይህ ትክክለኛ ሃይማኖት ነው: ይህ ነው ሃይማኖት ማለት: ማንኛውም ሃይማኖት የሂንዱም ሆነ:የእስልምና:ወይንም የክርስትና: የአምላክ ፍቅር እንዲኖረን ማድረግ ከተቻለ:ሃይማኖታችሁን በትክክል ይዛችኋል ማለት ነው: