AM/Prabhupada 0030 - ክርሽና ሁልግዜ በመደሰት ላይ ይገኛል፡፡

The printable version is no longer supported and may have rendering errors. Please update your browser bookmarks and please use the default browser print function instead.


Sri Isopanisad, Mantra 2-4 -- Los Angeles, May 6, 1970

አምላክ በመንፈሳዊ አለሙ ውስጥ ተወስኖ ያለ ይሁን እንጂ: ከአእምሮአችን የበለጠ ፍጥነት ያለው ሁኖ ይገኛል: በፍጥነቱ ከማንም በላይ ሁኖ ይገኛል:ትላልቅ ሃይል ያላቸው መላእክቶች እንኳን በቀላሉ ሊቀርቡት አይችሉም: በመንፈሳዊ አለም በአንድ ቦታ ተወስኖ ቢሆንም እንኳን:አየር:ውሃ የሚያቀርቡትን መላእክቶች ሁሉ ይቆጣጠራል: በባህሪው ከሁሉም በላይ እና ፍጹም ሁኖ ይገኛል: ይህም በብራህማ ሰሚታ ውስጥ ተጠቅሷል:“ጎሎካ ኤቫ ኒቫሳቲ አክሂላትማ ብሁታ” ክርሽና በጎሎካ ቭርንዳቨንም ውስጥ ይሁን እንጂ:ምንም የሚሰራው ነገር የለም: ከሚጎዳኛቸው ጋር ሁልግዜ ግዜውን በደስታ እያሳለፈ ነው: ይህም ከጎፒዎቹ ጋራ:ከእረኛ ጓደኞቹ ጋር:ከእናቱ ጋር:ከአባቱ ጋር ማለት ነው: እርሱም ሙሉ ለሙሉ ነጻ ነው:ከእርሱ ጋር ያሉትም ጓደኞቹ ደግሞ ከእርሱ በላይ ነጻ ናቸው: ይህም የሚሆንበት ምክንያት:የክርሽና ጓደኞች ለአደጋ ሲጋለጡ:ክርሽና እነሱን ለማዳን ጭንቅ ውስጥ ይገባል: ጓደኞቹ ግን ምንም ጭንቅ የላቸውም: “ክርሽና ስለአለ ምንም ችግር አይኖረንም” ብለው ያስባሉ: አያችሁት? ጓደኞቹ ምንም ጭንቀት የላቸውም: አንድ ነገር ሊከሰትባቸው ይችላል:የክርሽና መጽሃፍን ስታነቡ ብዙ አደጋዎች ተከስተው እንደነበረ ትረዳላችሁ: እረኛ ልጆቹ እና ክርሽና በቀን በቀን ላሞቹን እና ጥጃዎቹን ይዘው ወደ ጫካ ይሄዱ ነበር: በጫካው ውስጥ እና በያሙና ወንዝ ዳርም ይጫወቱ ነበር: ካምሳ ደግሞ እነርሱን ለመግደል የተለያዩ ሰይጣናሞች ይልክ ነበር: እና ይህን አይታችኋል:ስእሎችም አይታችኋል: እና ጓደኞቹ በክርሽና ብዙ እምነት ስለአላቸው: ዝም ብለው ይደሰቱ ነበር: ይህ መንፈሳዊ ኑሮ ነው:“አቫሽያ ራክሲቤ ክርሽና ቪሽቫሻ ፓላና” ይህም ጥልቅ የሆነ እምነት:“በምንም አደጋ ላይ ክርሽና ሁልግዜ ያድነኛል” ብሎ ማሰብ ለአምላክ መማረክ ነው ማለት ነው: ስድስት አይነትም የመማረክ አይነቶች አሉ: በመጀመሪያ ደረጃ:ለመንፈሳዊ አገልግሎት የሚያቀና ወይንም የሚያመቸውን ነገር ሁሉ መቀበል አለብን: ለመንፈሳዊ አገልግሎት እንቅፋት የሚሆነውን ነገር ሁሉ ደግሞ ማስወገድ አለብን: ቀጥሎ ደግሞ:መንፈሳዊ ከሆኑ ሰዎች ጋር ሁሉ መቅረብ እና መጎዳንኘት ያስፈልጋል: ክርሽና:ብዙ ጓደኞች አሉት: በመንፈሳዊ አለምም ወደ ፊት ስትራመዱ:ከክርሽና ጋር ያላችሁን ግኑኝነት በደንብ ልትረዱ ትችላላችሁ: ከዚያም እራሳችሁን ከዚያ መንፈሳዊ ጓደኝነት ማስተዋወቅ አለባችሁ: ከዚያም የሚቀጥለው ደግሞ:ክርሽና ከችግር ይጠብቀኛል ብሎ ሙሉ በሙሉ መተማመን ነው: ነገር ግን እርሱ ሁሉም ከመከራ እየጠበቀ ነው:ይህም የተረጋገጠ ነው: ነገር ግን በማያ ውስጥ ሁነን:እኛ እራሳችንን እንደምንጠብቅ እና እራሳችንን እንደምንመግብ አድርገን እናምናለን:(አምላክ ሳይሆን) አይደለም: ይህ ትክክል አይደለም: