AM/Prabhupada 0032 - ለመናገር የምፈልጋቸው ነገሮች ሁሉ በመፅሀፍቶቼ ተነግረዋል፡፡

The printable version is no longer supported and may have rendering errors. Please update your browser bookmarks and please use the default browser print function instead.


Arrival Speech -- May 17, 1977, Vrndavana

ፕራብሁፓዳ:“ለመናገር እያዳገተኝ ነው” በጣም ድክመትም እየተሰማኝ ነው: ወደ ሌላ ቦታም መሄድ ነበረብኝ:ወደ ቻንዲጋርህ ፕሮግራም: ነገር ግን ድክመት ስለሚሰማኝ ሰርዤዋለሁ: የጤናዬ ጉዳይ በጣም እየወደቀ ነው: ስለዚህም ወደ ቭርንዳቫና መምጣት ወስኛለሁ: ሞትም ከመጣ እዚህ ቢመጣ ይሻለኛል: ከዚህ ሌላ ለማለትም የሚያስፈልግ ነገር አይኖርም: መናገር የሚያስፈልገኝን ሁሉ: በመጽሃፎቼ ተናግሬአቸዋለሁ: አሁን እናንተ ተረድታችሁት:የእናንተን እርምጃ ቀጥሉ: እኔ እዚህ ምድር ላይ ኖርኩም አልኖርኩም ምንም ለውጥ አያመጣም: ክርሽና ለዘለአለም ነዋሪ እንደመሆኑም: እንደዚሁም ነፍስ ለዘለአለም ነዋሪ ናት: ነገር ግን: “ኪርቲር ያስያ ሳ ጂቫቲ” አንድ አማላክን በደንብ ያገለገለ ሰው ለዘለአለም ነዋሪ ነው: እናንተም እንዴት ክርሽናን እንደምታገለግሉ ተምራችኋል: እንዲሁም ከክርሽና ጋር ለዘለአለም እንኖራለን: ህይወታችን ዘለአለማዊ ናት: “ና ሃንያቴ ሃንያማኔ ሻሪሬ” (ብጊ 2 20) ይህ ገላ ለጊዜው ቢጠፋ: ምንም ችግር የለውም: ገላ ጠፊ ወይንም ሟች ነው: "ታትሃ ዴሃንታራ ፕራፕቲህ“ (ብ ጊ 2 13) ስለዚህ:ክርሽናን እያገለገላችሁ ለዘልአለም ኑሩ: በጣም አመሰግናለሁ: አገልጋዮች ”ጃያ“