AM/Prabhupada 0035 - በዚህ ገላችን ውስጥ ሁለት ዓይነት ዓብይ ነዋሪ ነፍሳቶች አሉ፡፡

The printable version is no longer supported and may have rendering errors. Please update your browser bookmarks and please use the default browser print function instead.


Lecture on BG 2.1-11 -- Johannesburg, October 17, 1975

አሁን ክርሽና የጉሩን (መንፈሳዊ መምህር) ደረጃ ይዞ: ማስተማር እና መምራት ጀመረ:: "ታም ኡቫቻ ርሺኬሻ" ርሺኬሻ: ሌላው የክርሽና ስም "ርሺኬሻ" ይባላል:: ርሺኬሻ ማለት: "ርሺካ ኢሻ" ርሺካ ማለት ስሜቶች ማለት ነው:: "ኢሻ" ማለት ነግሞ: ጌታ ወይንም የበላይ ማለት ነው:: ስለዚህ ክርሽና የስሜቶቻችን ሁሉ ጌታ ነው:: የሁላችንም ሰሜቶች ሁሉ የበላይ ተቆጣጣሪ:: ይህም በ13ኛ ምዕራፍ ተገልጿል:: "ሼትራ ግናም ቻፒ ማም ቪድሂ ሳርቫ ሼትሩ ብሃራታ (ብጊ 13 3 ) በዚህ በገላችን ውስጥ: ሁለት አይነት ነፍሶች አሉ:: አንዱ እኔ ራሴ ነኝ: የእኔ የራሴ ነፍስ ማለት ነው:: "አትማ" ይባላል:: ሌላው ደግሞ ክርሽና ወይንም "ፓራም አትማ" ይባላል:: "ኢሽቫራ ሳርቫ ብሁታናም ህርዴሼ አርጁና ቲስትሃቲ" (ብጊ 18 61) የዚህ ገላ ዋናው ባለቤት ግን "ፓራም አትማ" (ፈጣሪ) ነው:: ይህንን ገላ በአምላክ እንድገለገልበት ነው የተሰጠኝ: አለኝ ብዬ የማስባቸው ስሜቶች ሁሉ ደግሞ የእኔ ስሜቶች አይደሉም:: እጄን የፈጠርኩት እኔ አይደለሁም:: እጄ የተፈጠረው በአማላክ ወይንም በክርሽና ነው:: የተፈጠረውም በተፈጥሮ የአምላክ አገልጋዮች ነው:: እጄም የተሰጠኝ ለራሴ ለሚሆን ነገር እንድጠቀምበት ነው:: ይህም እንድበላበት: እንለቅምበት ነው:: ቢሆንም ግን የእኔ እጅ አይደለም:: ይህ እጃችን ፓራላይዝድ ከሆነ በኋላ ሁሉ: "እጄ" እንላለን:: ነገር ግን ልንጠቀምበት አንችልም:: ምክንያቱም ለመጠቀም የምንችልበትን ሃይል ባለቤቱ ወስዶታል (ፓራሊሲስ) ልክ ኪራይ ከፍላችሁ እንደምትኖሩበት ቤት ማለት ነው:: የቤቱ ባለቤት ከአባረባችሁ: ለመኖር አትችሉም: ቤቱን ልትጠቀሙበት አትችሉም:: እንደዚሁም ሁሉ: ይህንን ገላ ልንጠቀምበት የምንችለው: ዋናው ባለቤቱ ፈጣሪ ጌታ "ህርሺኬሻ" እስከፈቀደልን ግዜ ብቻ ነው:: ስለዚህ የክርሽና ስም "ርሺኬሻ" ተብሎ ይታወቃል:: ይህም የክርሽና ንቃተ ማህበር ማለት: ስሜታችንን ከክርሽና ተቀብለናል ማለት ነው: እነዚህም ስሜቶች ክርሽናን ለማገልገል እንጠቀምባቸዋለን: በአለማዊ ኑሮ ግን: ስሜታችንን ለክርሽና አገልግሎት ከመጠቀም ለራሳችን ጥቅም እናውለዋለን ማለት ነው: ይህ ነው የእኛ የስቃይ ኑሮ: ልክ የቤት ኪራይ እንደምትከፍሉበት ቤት ማለት ነው: ኪራይ የማትከፍሉ እና ይህ የእኔ ቤት ነው ብላችሁ የምታስቡ ከሆነ: ችግር ይመጣባችኋል: እንደዚሁም ሁሉ “ርሺኬሻ” ማለት ትክክለኛው ባለቤት ክርሽና ነው ማለት ነው: ይህን ንብረት ተሰጥቶኛል ብለን ማሰብ አለብን:ይህም በብሃጋቨድ ጊታ ተገልጿል: “ኢሽቫራ ሳርቫ ብሁታኒ ህርዴሼ አርጁና ቲስትሃቲ ብህራማያን ሳርቫ ብሁታኒ ያንትራሩድሃኒ ማያያ (ብጊ 18 61) ያንትራ ማለት ማሽን ማለት ነው:ይህ ማሽን ለእኔ በክርሽና ተሰጥቶኛል ይህንንም ያገኘሁት እንዲህ አይነት ማሽን ቢኖረኝ: እንዲህ አድርጌ መደሰት እችላለሁ ብዬ አስብ ስለነበረ ነው: ስለዚህም ክርሽና እንደ ፍላጎታችን ያሰብነውን ያሟላልናል: እንዲህም ካሰብን ደግሞ: ”ከሌላ እንስሳ ደም የምመጥበትን ገላ እፈልጋለሁ“ ካለን ደግሞ: ክርሽና እንዲህ ይለናል :”አሁን የነብር ገላ ውሰድ እና ተጠቀምበት“ ይለናል: እና ይህ ሁሉ እየተካሄደ ነው:ስለዚህም የክርሽና ስም ”ርሺኬሻ“ ይባላል: እንደዚህም ብለን መረዳት አለብን :”እኔ የዚህ ገላ ባለቤት አይደለሁም“ ክርሽና የገላችን ባለቤት ነው:እኔ ግን ስሜቴን የማስደስትበትን ገላ ለማግኘት እሻለሁ: ገላውን ሰጥቶናል ነገር ግን ደስታኛ ላንሆን እንችላለን: ስለዚህ ይህን ገላ ለባለቤቱ እንድንጠቀምበት ያስፈልጋል:ይህም ”ብሃክቲ“ ወይንም በፍቅር የሚሰራ የአማላክ አገልግሎት ይባላል: ”ህሪሺኬሻ ርሺኬሻ ሴቫናም ብሃክቲር ኡቻቴ“ (ቼቻ ማድህያ 19 170) ስሜቶቻችን ለማገልገል መጠቀም ነው:ምክንያቱም ክርሽና የስሜቶቻችን ሁሉ ባለቤት ነው: የገላችንም ባለቤት ነው: ይህም ገላ ለባለቤቱ ለአማላካችን ስንገለገልበት ይህ የህይወታችን መሳካት ነው ማለት ነው: