AM/Prabhupada 0036 - የሕይወታችን ዓላማ፡፡

The printable version is no longer supported and may have rendering errors. Please update your browser bookmarks and please use the default browser print function instead.


Lecture on BG 2.1-11 -- Johannesburg, October 17, 1975

ይህም አለማዊ ኑሮአችን: እንቆቅልሽ ሁኖ ግራ ሲያጋባን: ምን ማድረግ እና: ምን አለማድረግ እንዳለብን ለመረዳት ሲያዳግተን: በዚያንም ግዜ ጉሩ (መንፈሳዊ መምህር) መቅረብ አለብን: ይህን ትእዛዝ ነው እዚህ የምናየው: "ፕርቻሚትቫም ድሃርማ ሳሙድሃ ቼታሃ" ኑሮ ግራ ሲያጋባን: የትኛው ሃይማኖታዊ እና ሃይማኖታዊ ያልሆነውን መለየት ያዳግተናል: ያለንንም ደረጃ በአግባቡ አንጠቀምበትም: ይህም እንዲህ ይባላል: "ካርፓንያ ዶሻፓሃታ ስቫብሃቫ (ብጊ 2 7) በዚህም ግዜ ጉሩ ያስፈልገናል: ይህ ነው የቬዲክ ቅዱስ መጻህፍት ትእዛዝ: "ታድ ቪግናናርግሃም ሳ ጉሩም ኤቫብሂጋቼት ሽሮትሪያም ብራህማ ኒስትሃም" (ሙኡ 1 2 12) ይህ ነው ሃላፊነት ማለት: ይህ ነው ሥልጣኔ ማለት: በህይወታችን ብዙ አይነት ፍዳዎች ያጋጥሙናል: ይህ በተፈጥሮ ያለ ነው:: ይህም አለም በተለያዩ ችግሮች የተሞላ ነው:: "ፓዳም ፓዳም ያድ ቪፓዳም" (ሽብ 10 14 58) አለማዊ ህይወት ላይ: በየእርምጃችን አደጋ ሊያጋጥመን ይችላል ማለት ነው: ይህ የአለማዊ ህይወት መሰረቱ ነው: ስለዚህም ከጉሩ መመሪያ መውሰድ አለብን:: ከአስተማሪው: ከመንፈሳዊ አባታችን: በህይወታችን ላይ እንዴት በቀና እንደምንራመድ መማር አለብን: ይህም በኋላ በደንብ ይገለጻል:: የህይወታችን መድረሻ አላማ: ቢያንስ በዚህ በያዝነው የሰው ልጅ ህይወታችን: እንዴት ማድረግ እንደሚገባን በአርያን ስልጣኔ: ተገልጾልናል:: የህይወታችን መድረሻ አላማ: የነፍሳችን መሰረታዊ ደረጃ ምን እንደሆነን መረዳት ነው:: "ማነኝ እኔ?“ ምንድን ነኝ?” እኔ (ነፍሴ)ምን እንደሆንኩኝ የማላቅ ከሆነ ግን:እኔም ከድመቶች እና ከውሾች አልሻልም ማለት ነው: ውሾች እና ድመቶች የነፍሳቸው ሚና ምን እንደሆነ አያውቁም:የሚያስቡትም ገላቸው እንደሆኑ ነው እንጂ ነፍሳቸው ምን እንደሆነች አያውቁም: ይህ ሁሉ ይተነተናል:ስለዚህ በህይወታችን ኑሮ እንቆቅልሽ ሁኖ ግር የሚለን ደረጃ ላይ ስንደረስ: (በመሰረቱ ሁላችንም በህይወት እንቆቅልሽ ላይ ነው ያለነው): ስለዚህ ወደ ትክክለኛውን ጉሩ ለትምህርት መቅረብ አለብን: አሁን እንደምናየው:አርጁና ክርሽናን ቀርቦታል:አንደኛ ደረጃ ጉሩ:እርሱም የአንደኛ ደረጃ መምህር ነው: ዋናው ጉሩ ማለት ታላቁ ጌታ አምላካችን ነው:እርሱም የሁሉም ጉሩ ነው:“ፓራም ጉሩ” እንደዚሁም ሁሉ ማንም ሰው ክርሽናን በትክክል የሚወክል ከሆነ:እርሱም ጉሩ ነው ይባላል: ይህም በአራተኛው ምዕራፍ ተገልጿል: “ኤቫም ፓራማፓራ ፕራፕታም ኢማም ራጃርሳዮ ቪዱህ” (ብጊ4 2) ክርሽናም በምሳሌ አስረድቶናል:ይህም ወዴት ልቦናችንን ለመስጠት እንደሚገባን እና: ማንን እንደ ጉሩ መቀበል እንዳለብን ሁሉ በምዕራፎቹ ተገልጿል: ክርሽና እዚህ አለ:(በብሃጋቫድ ጊታ ቅዱስ መጽሃፍ)ስለዚህ ክርሽናን ተቀብላችሁ መከተል አለባችሁ ወይንም የእርሱን ተወካይ ጉሩን መከተል ነው: በዚህም ግዜ የህይወት እንቆቅልሻችሁ ሁሉ ይፈታል: አለበለዛ ግን ይህን መፍታት አዳጋች ነው:ምክንያቱም ጉሩ ብቻ ነው ምን ለእናንተ ጥሩ የሚሆነውን እና መጥፎ የሚሆነው ሊነግራችሁ የሚችለው: እንዲህም ብሎ ጠይቋል:“ያክ ሽሬያህ ስያን ኒሽቺታም ብሩሂ ታት (ብጊ 2 7)”ኒሽቺታም“ ምክር እና መመሪያ ከፈለጋችሁ:”ኒሽቺታም“ ጥርጥር እና ምትሃት የሌለው: ስህተት የሌለው እና ማታለል የማይገኝበት መመሪያ ”ኒሽቺታም“ ይባላል: ይህንንም ለማግኘት የምትችሉት ወይ ከክርሽና ወይ ከተወካዩ ነው: ትክክለኛ የሆነ መረጃ:እንከን ካለው ሰው ወይንም አታላይ ሰው ማግኘት አይቻልም: ይህም ሰው ትክክለኛ ትእዛዝን ሊሰጠን አይችልም: በአሁኒ ግዜ ጉሩ መሆን እንደ ፋሽን ሁኖአል: እነዚህም የዘመኑ ጉሩዎች:የራሳቸውን ግምገማ ይሰጣሉ:”እኔ እንደሚመስለኝ ከሆነ“ ”በእኔ አስተያየት“ ብለው ይናገራሉ: ይህ ጉሩ ሊሆን አይችልም:ጉሩ ማለት የሻስትራን የቅዱስ መጽሃፎችን ጥቅስ እየጠቀስ ማርጃ ማቅረብ አለበት: ”ያህ ሻስትራ ቪድሂም ኡትስርጅያ ቫርታቴ ካማ ካራታሃ“ (ብጊ16 23) ማንም ሰው ከሻስትራ ቅዱስ መፃህፍቶች ጥቅስ እያወጣ መረጃ የማያቀርብ ከሆነ: ”ና ሲዲሂም ሳ አቫፕኖቲ“ እንዲህ አይነት ሰው በማናቸውም ግዜ አገልግሎቱ የተሳካ ሊሆን አይችልም: ”ና ሱክሃም“ በዚህ አለም ላይም ምንም ደስታ ሊያገኝ አይችልም: “ና ፓራም ጋቲም” ወደ ከፍተኛው መንፈሳዊ አልሙን መተላለፍ ይቅርና:ይህ ነው የሻስትራ ትእዛዝ: