AM/Prabhupada 0038 - እውቀት የሚገኘው ከቬዳዎች ስነፅሁፍ ነው፡፡

The printable version is no longer supported and may have rendering errors. Please update your browser bookmarks and please use the default browser print function instead.


Lecture on BG 7.1 -- Hong Kong, January 25, 1975

አሁን ክርሽና እዚህ አለ:: አሁን የክርሽና ስእሎች አሉን: የክርሽና ፎቶዎች አሉን: የክርሽና ቤተመቅደሶች አሉን: ስለ ክርሽና ብዙ ነገሮች አሉን: እነዚህም ልብ ወለዶች አይደሉም:: ከሃሳባችን የመነጩም አይደሉም:: እንደ "ማያቫዲ" ፈላስፋዎች "በሃሳብህ እንደልብህ አምላክን መመሰል ትችላለህ" እንደሚሉት አይደለም:: አይደለም:: ፈጣሪ አምላክ በሃሳባችን ገምተን ሊመሰል አይችልም:: ይህ ሌላ ሞኝነት ነው:: እንዴት አድርጋችሁ የአምላክን ምሰል በግምት መመሰል ትችላላችሁ? እንዲህ ከሆነማ: ፈጣሪ አምላክ: በሃሳባችን የተፈጠረ አምላክ ይሆናል: ይህ ምንም ጥሬ ነገር የለውም:: ይህ አምላክ ሊሆን አይችልም:: በሃሳብ ተገምቶ የተፈጠረ አምላክ ሊሆን አይችልም:: ፈጣሪ አማላክ በፊት ለፊታችን ለመቅረብ የሚችል ነው:: ክርሽና በዚህ ምድር ላይ መጥቷል: “ታዳትማናም ስርጃሚ አሃም ሳምብሃቫሚ ዩጌ ዩጌ” ፈጣሪ አምላክን ያዩ ሰዎች: ይኖ ራሉ: ከእነርሱም መረጃ መውሰድ ትችላላችሁ: “ታድቪድሂ ፕራኒፓቴና ፓሪፕራሽኔና ሴቫያ ኡፓዴክሽያንቲ ቴ ግያናም ግያኒናስ ታትቫ ዳርሺና (ብ ጊ 4 34) ”ታትቫ ዳርሺና“ እራስህ ያላየህ ከሆነ: እንዴት ለሌላው መረጃ መስጠት ትችላለህ? እንደዚህም ፈጣሪ አምላክ በምድር ላይ ታይቷል:በታሪክ ብቻ አይደለም የተሰማው: ክርሽና በዚህ ምድር ላይ በነበረ ግዜ: ስለ ”ኩሩክ ሼትራ“ ታላቁ ጦርነት በታሪክ በደንብ ተተንትኖ ተጽፏል: ይህ ብሃጋቫድ ጊታም በዚህን ግዜ እንዴት እንደተነገረ በታሪክ በግልጽ ተተንትኖ ተጽፏል: ይህንን ሁሉ በታሪክ: በብሃጋቫን ሽሪ ክርሽና እና በሻሽትራ ቅዱስ መጽሃፎች መረዳት እንችላለን: ”ሻሽትራ ቻክሹስ“ በቅዱስ መጽሃፎች መረጃዎች ማየት: ልክ እንደ አሁኑ ግዜ: ክርሽና በአካሉ በምድር ላይ አይገኝም: ነገር ግን በእነዚህ በቅዱስ መፃህፍቶች ክርሽና ማን እንደሆነ መረዳት እንችላለን: ስለዚህ ”ሻስትራ ቻክሱሳ ሻስትራ" ወይ በቀጥታ መማር አለብን ወይንም ደግሞ ከሻስትራ ወይንም ቅዱስ መፃህፍቶች መማር አለብን: በግል ከምንማረው ደግሞ ከሻስትራ በቀጥታ የምንማረው የበለጠ ነው: የእኛም መንፈሳዊ እውቀት: የቬዲክ መመሪያዎችን የሚከተሉ ሁሉ: እውቀታቸው ሁሉ የሚመነጨው: ከቬዳ ቅዱስ መፃህፍቶች ነው: የቬዲክ እውቀትን ከሃሳባቸው በግምት አያመርቱትም: አንድ በቬዳ የተረጋገጠ ነገር:ሁል ግዜ እርግጠኛ ሁኖ ይገኛል: ክርሽናን በደንብ ልንረዳው የምንችለው በቬዳዎች ቅዱስ ስነፅሁፎች ነው: “ቬዳሽ ቻ ሳርቬይር አሃም ኤቫ ቬድያህ” (ብጊ15 15) ይህም በብሃጋቫድ ጊታ በደንብ ተገልጿል:ክርሽናን በሃሳባችሁ ልትገምቱት አትችሉም: ተንኮለኞች በሃሳባችን አምላክ ምን እንደሆነ እንገምታለን ቢሉ ይህ ተንኮለኝነት ነው: ክርሽናን ለማየት የምትችሉት የቬዳን ቅዱስ መፃህፍቶች በማንበብ በው: “ቬዳይሽ ቻ ሳርቬር አሃም ኤቫ ቬድያህ” (ብጊ 15 15) ይህ ነው የቬዳዎች አላማ: ስለዚህም “ቬዳንታ” ተብለው ይጠራሉ: የክርሽና እውቀት “ቬዳንታ” ነው: