AM/Prabhupada 0040 - አንድ አብዩ ጌታ እዚህ አለ፡፡

The printable version is no longer supported and may have rendering errors. Please update your browser bookmarks and please use the default browser print function instead.


Lecture on BG 16.8 -- Tokyo, January 28, 1975

በዚህ አለም ላይ: በሚሊዮን እና በትሪልዮን የሚቆጠሩ: ነዋሪ ነፍሳቶች አሉ:: ፈጣሪ አምላካችንም በእያንዳንዱ ነፍስ ልብ ውስጥ: ተቀምጦ ይገኛል:: "ሳርቫስያ ቻሃም ህርዲ ሳኒቪስቶ ማታ ስምርቲር ጅያናም አፖሃናምቻ" (ብጊ 15 15) አምላክ እንዲህ እያደረገ እያስተዳደረን ይገኛል:: ታድያ: ፈጣሪ አምላካችን: እንደኛ የሚቆጣጠር ነው: ብለን እራሳችንን ከእርሱ ጋር ማወዳደር: ይህ የእኛ ድንቁርና ነው:: ፈጣሪ አምላክ ሁሉን የሚቆጣጠር ነው:: የአለም ሁሉ ተቆጣጣሪ አለ ማለት ነው:: አምላክም ሊቆጣጠር የሚችለው: ወሰን በሌለው እውቀቱ: ወሰን በሌለው አገልጋዮቹ: እና ወሰን በሌለው ሃይሉ ነው:: እነዚህ በአምላክ ሰብአዊ መንፈስ የማያምኑ: (በህንድ የሚገኙ) የአምላክ ሰብአዊ መንፈስ ምን ያህል ሃይል እንዳለው ማመን በጣም ያዳግታቸዋል:: ስለዚህም የሰብአዊ መንፈስ ከሃዲዎች ሁነው ይገኛሉ:: ይህን ሰብአዊነት ለማስተዋል በጣም ያዳግታቸዋል:: እነዚህ በአምላክ ሰብአዊነት የማያምኑ: ይህንን ማሰብ በጣም ያዳግታቸዋል:: እነሱም የሚያስቡት: "አንድ ሰው እንደ ሰው ከሆነ: እንደኔ ሰው መሆን አለበት" ብለው ያምናሉ:: እኔ ይህን ማድረግ ካልቻልኩኝ: እርሱም እንደዚህ ማድረግ አይችልም: ብለው ያምናሉ:: ስለዚህም: "ሙድሃ" ተብለው ይጠራሉ:: "አቫጃናንቲ ማም ሙድሃህ (ብጊ 9 11) ክርሽና አምላክን ከእነርሱ ጋር ያወዳድሩታል:: እርሱ ሰው እንደመሆኑም ሁሉ: አምላካችን ክርሽናም ፈጣሪ ሰው ነው:: ስለዚህ እውቀት የላቸውም:: የቬዳ ቅዱስ ስነፅሁፎች እንዲህ ብለው ያስረዱናል: "ፈጣሪ አምላክ ሰው ይሁንም እንጂ: ወሰን የሌለው የሰዎች ብዛትን ሲያስተዳድር ይገኛል" ይህን እነዚህ ሰዎች ሊረዱ አይችሉም:: "ኤኮ ባሁናም ቪዳድሃቲ ካማን" ይህ አንዱ ፈጣሪ ሰው: በብዙ ሚልዮን እና ትሪሊዮን የሚቆጠሩትን ሰዎች ሲያስተዳድር ይገኛል:: እኛ እያንዳንዳችን ሰዎች ነን:: እኔ ሰው ነኝ: አንተም ሰው ነህ:: ጉንዳን ሰብአዊ ነው: ድመት ሰብአዊ ናት: ውሻ ሰብአዊ ነው: ተባይ ሰብአዊ ነው: ዛፎች ሰብአዊ ናቸው: ሁሉም ነፍሳት ሰብአዊ ናቸው:: ሌላም ደግሞ ሰብአዊ ፍጡር አለ:: ይህም አምላካችን ፈጣሪ ክርሽና ነው:: ይህ አንድ ሰብአዊ ፍጡር: ወሰን በሌለው ሃይሉ: በሚልዮን እና በትሪልዮን የሚቆጠሩትን ሰዎች ሲያስተዳድር ይገኛል:: ይህም በቬዲክ ቅዱስ ስነፅሁፎች ተገልጿል:: "ኤኮ ባሁናም ቪዳድሃቲ ካማን ኒትዮ ኒትያናም ቼታናስ ቼታናናም (ካትሃ ኡፓኒሻድ 2 2 13) ይህ ነው መግለጫው:: ክርሽናም በብሃጋቫድ ጊታ እንዲህ አለ: "አሃም ሳርጋስያ ፕራብሃቮ ማታህ ሳርቫም ፕራቫርታቴ ኢቲ ማትቫ ብሃጃንቴ ማም (ብ ጊ 10 8) ስለዚህም የክርሽና አገልጋዮች ይህንን በትክክል ሲረዱ "አምላክ አንድ ብቻ መሆኑን ሲረዱ" "አምላክ የሁሉም መሪ እንደሆነ: የሁሉም ተቆጣጣሪ እንደሆነ: የሁሉም አስተዳዳሪ እንደሆነ" ለመረዳት ሲችሉ: በቀላሉ ሙሉ ልቦናቸውን ለመስጠት እና: ትሁት የአማላክ አገልጋር መሆን ይችላሉ::