AM/Prabhupada 0043 - ብሀገቨድ ጊታ መሰረታዊ መመሪያችን ነው፡፡

The printable version is no longer supported and may have rendering errors. Please update your browser bookmarks and please use the default browser print function instead.


Lecture on BG 7.1 -- Sydney, February 16, 1973

Prabhupāda:

“ዮጋም ዩንጃን ማድ አሽራያሃ አሳምሻያም ሳማግራም ማም ያትሃ ግናስያሲ ታክ ችርኑ” (ብጊ 7 1) ይህ ጥቅስ የመጣው ከብሃገቨድ ጊታ ነው: የሚያስተምረንም እንዴት የክርሽናን ንቃት ወይንም የፈጣሪ አማላክን ንቃት እንዴት እንደምናዳብር ነው: “ብሃገቫድ ጊታ” ብዙዎቻችሁ ስለዚህ ቅዱስ መጽሃፍ ስም ሰምታችኋል: በአለም ላይ በጣም ከፍ ባል ቁጥር ህዝብ የሚነበብ መጽሃፍ ነው: በአለም ላይ በእየአንዳንዱ አገር የተለያዩ:የታተሙ የብሃገቫድ ጊታ መጻህፍቶች ይገኛሉ: ይህም ብሃገቨድ ጊታ:የእኛ የክርሽና ንቃተ ማህበር ዋናው መመሪያ መጽሃፍ ነው: የክርሽና ንቃት ብለን የምናስፋፋው ሁሉ:የዚሁን የብሃገቨድ ጊታን መልእክት ብቻ ነው: እራሳችን የፈለሰፍነው ነገር የለም: ይህ የክርሽና ንቃት:ምድር ከተፈጠረች ግዜ ጀምሮ የነበረ ነው: ቢያንስ እንኳን ለአለፉት 5000 ዐመታት:ክርሽና መጥቶ ከነበረበት ግዜ ጀምሮ ማለት ይቻላል: ክርሽና እራሱ ይህንን የክርሽና ንቃት በምድር ላይ መርቶ አስተምሮናል: ትቶልን የሄደውም ትምህርት እና መንፈሳዊ ትእዛዛት:ይኅው በዚህ በብሃጋቨድ ጊታ ተመዝግቧል: ቢሆን ግን:ይብ ብሃገቨድ ጊታ: በአዋቂ ነኝ ባዮች እና በስዋሚ (መነኩሴ)ነኝ ባዮች:በተለያየ መንገድ አለአግባብ ተተርጉሞ ይገኛል: እንዚህም በፈጣሪ ሰብአዊነት የማያምኑ እና በፈጣሪ የማያምኑ ሰዎች ተርጉመውት ነው: ብሃገቨድ ጊታንም የተረጎሙት:የራሳቸውን ትርጉም በመስጠት ነው: በ1966 አሜሪካ ውስጥ እያለሁ:አንድ አሜሪካዊ ሴትዮ ጠይቃኝ ነበር: ይህም የጠየቀችኝ:የየትኛውን የብሃገቨድ ጊታ መጽሃፍ ህትመት ለማንበብ እንድመራት ነበር: እውነቱን ለመናገር ግን: የትኛውንም ህትመት እንድታነብ ለመምራት አልቻልኩም: ይህም ይትርጉሙ አቀራረብ የአማራቸውን የግል አሰተያየት ሞልተውበት ስለነበረ ነው: ይህም ብሃጋቫድ ጊታ ልክ በክርሽና እንደተዘመረው ወይንም እንደተናገረው የሚተረጉምን መጽሃፍ እንዳሳትም ገፋፋኝ: ይህ አሁን የምታዩትም ህትመት:”ብሃገቨድ ጊታ እንደ ተዘመረው“ በማክሚላን ካምፓኒ በአለም ታላቁ መጽሃፍ አታሚ ታትሞ ይገኛል: እንደዚህም እያደረግን በጥሩ ሁኔታ እየተራመድን እንገኛለን: በመጀመሪያ ያተምነውም የትንሿ መጽሃፍ የ “ብሃገቫድ ጊታ እንደ ተዘመረው”መጽሃፍ የታተመው በ1968 (አአ)አመተ ምህረት ነው: በከፍተኛ ደረጃም ይሸጥ ነበር: የማክሚላን ካምፓኒም የንግድ ማናጀሮችም ለእኛ ሪፖርት አደርገው ነበር: የእኛ መጽሃፎች ብዙ እየተሸጡ የሌሎች መጽሃፎችም ሽያጭ እየቀነሰ መሆኑን ተናግረዋል: ከዚያም በ1972 የሙሉ በሙሉ የ“ብሃገቨድ ጊታ እንደ ተዘመረው” መጽሃፍን ተርጉመን አሳተምን: ማክሚላን ካምፓኒም 50000 መጽሃፍቶችን በቅድሚያ አሳትሞ አቀረበ: ይህም በ3 ወር ውስጥ ተሽጦ አልቆ እንደገና ለማሳተም መሯሯጥ ጀመርን: