AM/Prabhupada 0044 - አገልግሎት ማለት የጌታውን ትእዛዝ በትክክል ተከተሉ ማለት ነው፡፡

Revision as of 06:06, 29 November 2017 by Sahadeva (talk | contribs) (Text replacement - "<!-- END NAVIGATION BAR --> <!-- BEGIN ORIGINAL VANIQUOTES PAGE LINK-->" to "<!-- END NAVIGATION BAR --> <!-- BEGIN ORIGINAL VANIQUOTES PAGE LINK-->")
(diff) ← Older revision | Latest revision (diff) | Newer revision → (diff)


Lecture on BG 4.1 -- Montreal, August 24, 1968

ይህም ማለት:አጋልጋዩ:ክርሽናን የሚያሳየውን መንገድ እየተከተለ ማለት ነው:ይኅው ነው: አገልጋይ:ክርሽና እንደ እኔ ጠላት እንኳን ሁን ቢለው:በፍቅር ለማገልገል ሲል:ቅር አይለውም: ዋናው የፍቅር አገልግሎት ማለት የክርሽናን መመሪያ መከተል ነው: ክርሽና ”ጠላቴ ሁን“ ቢለኝ:ጠላቱ እሆናለሁ:ይህ በፍቅር የሚደረግ ትእዛዝን መከተል ነው: ይህም ክርሽናን ለማስደሰት የሚደረግ ነው:(ትእዛዝን በማክበር) ልክ አንዳንድ ግዜ:አለቃው አገልጋዩን ”እዚህ ጋ ምታኝ“ ሊለው ይችላል: እርሱም እዛው ጋ ቢመታው:ቃሉን አክብሮ አገለገለው ማለት ነው: ሌሎች ይህን ያዩ ግን:”ወይ ጉድ:አለቃውን እየመታው የሚያገለግል ይመስለዋል:ይህ ምን ጉድ ነው?“ ብለው ሊያስቡ ይችላሉ: ነገር ግን አለቃው እንዲመታው አዞታል: ይህም ማገልገል ነው: ማገልገል ማለት የአለቃውን ትእዛዝ ተከትሎ መፈፀም ማለት ነው: ምንም አይነት ስራ ቢሆንም: በጌታ ቼይታንያም ህይወት ላይ:አንድ ጥሩ ያየነው ምሳሌ አለ:ይህም ስለ አገልጋዩ ጎቪንዳ ስለሚባለው ነው: ጌታ ቼይታንያ ምሳውን ከጨረሰም በኃላም:ጎቪንዳ ምሳውን ይበላ ነበር: አንድ ቀንም:ጌታ ቼይታንያ ምሳውን ከበላ በኋላ:በበሩ መግቢያው ላይ ሸለብ እንዲለው ጋደም አለ: ምንድን ነው የሚባለው? በር? መግቢያ? ጎቪንዳም በላዩ ላይ ተራምዶ ገባ: ይህም ከምሳ በኋላ: ሁልግዜ ጎቪንዳ ማሳጅ ስለሚያደርገው ነው: ስለዚህም ጎቪንዳ: ተኝቶ የነበረውን ጌታ ቼታንያን በላዩ ተራምዶ:ማሳጅ ለድረግ ክፍሉ ውስጥ ገባ: ጌታ ቼታንያም ተኝቶ ነበር እና ከግማሽ ሰአት በኋላ ነቃ: ከእንቅልፍም ሲነሳ:ጎቪንዳ ክፍሉ ውስጥ ተቀምጦ አየው:እንዲህም አለው:”ጎቪንዳ እስከ አሁን ፕራሳዳም (ምሳ)አልበላህምን?“ እርሱም አልበላሁም አለ:ጌታ ቼይታንያም ለምን ብሎ ጠየቀው:እርሱም እንዲህ መለሰ:”አንተ ጋደም ብለህ ስለሆነ:መሻገር ጠልቼ ነው“ አለው: ”ታድያ እንዴት አድርገ ገባህ?“ ብሎም ጠየቀው:እርሱም ”ተሻግሬ ገባሁ“ ብሎ መለሰ: ”ታድያ ተሻግረህ እንደገባኅው ለምን ተሻግረህ አትወጣም ነበረ?“ ብሎ ጠየቀው: እርሱም እንዲህ አለ:“መጀመሪያ የተሻገርኩት አንተን ለማለልገል ነበር:አሁን ግን ለግል ጥቅሜ ምሳ ለመብላት:አንተን ተሻግሬ ለመሄድ አልችልም” ብሎ መለሰለት: ይህንንም ማድረግ አይገባኝም:ይህም ለአንተ ሳይሆን ለእኔ ጥቅም ስለሆነ ነው: እንደዚህም ሁሉ ለክርሽና ደስታ ብላችሁ:ጠላቱም:ጓደኛውም:ወይንም የተፈለገውን መሆን ትችላላችሁ: ይህም “ብሃክቲ ዮጋ” ይባላል: ምክንያቱም አላማችሁ ክርሽናን ለማስደሰት ብቻ ስለሆነ ነው: ልክ የእራሳችሁን ስሜቶች ማገልገል ስትጀምሩ ደግሞ:ወደ አለማዊ ኑሮ ወዲያውኑ ተመለሳችሁ ማለት ነው: “ክርሽና ባሂርሙክሃ ሃና ብሆጋ ቫንቻ ካሬ ኒካታ ስትሃ ማያ ታሬ ጃፓቲያ ድሃሬ (ፕሬማ ቪቫርታ) ክርሽናን ረስተን:የግላችንን ስሜቶች ለማስደሰት ስንጀምር:ይህ ”ማያ“ ይባላል: ይህንንም የራሳችንን ሰሜት ለማስደሰት የምንጥረውን መንገድ አቁመን: ሁሉንም ነገር ለክርሽና ስናደርግ ደግሞ: ይህም ነፃነት ይባላል: