AM/Prabhupada 0056 - በሻስትራ የቬዳ ሥነፅሁፎች ውስጥ አስራ ሁለት መንፈሳዊ ባለሥልጣኖች ተገልፀዋል፡፡

Revision as of 06:06, 29 November 2017 by Sahadeva (talk | contribs) (Text replacement - "<!-- END NAVIGATION BAR --> <!-- BEGIN ORIGINAL VANIQUOTES PAGE LINK-->" to "<!-- END NAVIGATION BAR --> <!-- BEGIN ORIGINAL VANIQUOTES PAGE LINK-->")
(diff) ← Older revision | Latest revision (diff) | Newer revision → (diff)


Lecture on SB 7.6.1 -- Madras, January 2, 1976

”ሽሪ ፕራህላዳ ኡቫቻ:ኮማራ አቻሬት ፕራግኖ ዳሃርማን ባሃጋቫታት ኢሃ“® ”ዱርላብሃም ማኑሻም ጃንማ ታድ አፒ አድህሩቫም አርትሃዳም (ሽብ 7 6 1) ይህ ፕራላድ ማሃራጃ ነው: እርሱም ለክርሽና ንቃት: አንዱ በጣም ትልቅ የሆነ: ባለ ሥልጣን ነው: በሻስትራ ቅዱስ ማጻህፍት ውስጥ: 12 አይነት ባለስልጣኖች ይገኛሉ: “ሽቫያምቡሃ ናራዳህ ሻምቡህ ኩማራሃ ካፒሎ ማኑህ” “ፕራህላዶ ጃናኮ ብሂሽሞ ባሊር ቫያሳኪር ቫያም” (ሽብ 6 3 20) እነዚህም በያመራጅ የተሰጠው:የድሃርማ (ሃይማኖት) ባለስልጣኖች ናቸው: ድሃርማ ማለት “ብሃጋቫድ ድሃርማ” ትላንትና እንደገለጽኩት ሁሉ:ድሃርማ ማለት ብሃጋቫታ ማለት ነው: “ድሃርማም ቱ ሳክሳድ ብሃገቫት ፕራኒታም” (ሽብ 6 3 19) ለምሳሌ ዋነኛው ዳኛ:ህግን ተከትሎ: ፍርዱን እንደሚሰጥ ሁሉ: እንደዚሁም:የመንግስት ህግጋት:በአንድ ሰው ወይንም በነጋዴ የሚደነገጉ አይደሉም: ህግ የሚደነገገው በመንግስት ብቻ ነው: ማንም ሰው ህግ መደንገግ አይችልም: በከፍተኛ ፍርድ ቤትም:አንድ ሰው ለዳኛው:እኔ የራሴ ህግ አለኝ ቢለውም:ዳኛው ሊቀበለው አይችልም: እንደዚሁም ሁሉ ድሃርማ (ሃይማኖት) እራሳችሁ ልትፈጥሩት አትችሉም: ትልቅ ሰው ብትሆኑ እንኳን: የፍትህ ሁሉ ዋና መሪ እንኳን ብትሆኑ:ህግ እራሳችሁ መደንገግ አትችሉም:ህግ የሚደነገገው በመንግስት ብቻ ነው: እንደዚሁም ሁሉ ድሃርማ (ሃይማኖት)ማለት“ብሃጋቫታ ድሃርማ” ወይንም በፈጣሪ የተደነገገ ማለት ነው: ሌሎችም ድሃርማ የሚሏቸው:ድሃርማ ሊሆኑ አይችሉም:ተቀባይነትም የላቸውም: በቤታችን የተደነገገ ህግ ሁሉ በመንግስት ተቀባይነት የለውም: ስለዚህ እንዲህ ተብሏል:“ድሃርማ ቱ ሳድሻድ ብሃጋቫት ፕራኒታም” (ሽብ6 3 19) እና ይህ “ብሃገቫት ፕራኒታም ድሃርማ” ምንድን ነው? ይህም በብሃገቨድ ጊታ ተገልጿል:እንደምናውቀውም: ክርሽና የመጣበትም አላማ:“ድሃርማ ሳምስትሃ ፓናርትሃያ” የሃይማኖትን መመሪያዎች ለማቋቋም እና:እንደገና ለማስተዋወቅ ነበር: “ድሃርማስያ ግላኒር ብሃቨቲ ብሃራታ” “ያዳ ያዳ ሂ ድሃርማስያ ግላኒር ብሃቨቲ ብሃረታ” (ብጊ4 7) አንዳንድ ግዜ በምድር ላይ “ግላኒ” ይኖራል:ይህም ሃይማኖትን ሲከተሉ እንከን ያለባቸው መንገዶችን ሲይዙ ነው: ያንንም ግዜ ክርሽና እዚህ ምድር ላይ ይመጣል:“ፓሪትራናያ ሳድሁናም ቪናሻያ ቻ ዱስክርታም” (ብጊ4 8) “ዩጌ ዩጌ ሳምብሃቫሚ” ክርሽና ሃሰታዊ የሆኑትን ድሃርማዎች ከፍ ለማድረግ አለመጣም: ሂንዱ ድሃርማ:ሙስሊም ድሃርማ:ክርስቲያን ድሃርማ:ቡድሃ ድሃርማ:አይደለም: በሽሪማድ ብሃገቨታም እንደተጠቀሰውም ሁሉ:“ድሃርማ ፕሮጂሂታ ካይታቮ” (ሽብ 1 1 2) ድሃርማ (ሃይማኖት)የማታለል ፈለግ ያለው ከሆነ: እንደዚህ የማታለል ባህርይ ያለው ድሃርማ “ፕሮጂታ” ይባላል: “ፕራክርስታ ሩፔና ኡጂታ” ማለትም ይህ መጣል አለበት ወይንም ማስወገድ አለብን: ትክክለኛ ድሃርማ:“ብሃጋቫድ ድሃርማ” ነው: ትክክለኛ ድሃርማ: ስለዚህም ፕራላድ ማሃራጃ እንዲህ አለ:“ኮማራ አቻሬት ፕራግኖ ድሃርማን ብሃጋቫታን ኢሃ” (ሽብ 7 6 1) ድሃርማ ማለት:አምላክ እና የእኛም ከአምላክ ጋር ያለን ግኑኝነት ማለት ነው: እንደዚሁም ሁሉ: በዚያ ግኑኝነት መቀጠል እና: የህይዋታችንን አላማ ማሳካት ማለት ነው: ይን ድሃርማ ይባላል: