AM/Prabhupada 0059 - ትክክለኛ ስራችሁን አትዘንጉ፡

The printable version is no longer supported and may have rendering errors. Please update your browser bookmarks and please use the default browser print function instead.


Lecture on BG 2.14 -- Mexico, February 14, 1975

ጥያቄውም እምዲህ ነው:“እኔ (ነፍሴ)ዘለአለማዊ ከሆንኩ:ለምንድን ነው ህይወት ብዙ ስቃይ የተሞላባት?” ለምንስ በግድ እንድሞት ተገደድኩ? ይህ የአዋቂ ሰው ጥያቄ ነው:“እኔ ዘለአለማዊ ከሆንኩኝ” “ለምን እዚህ አለማዊ ገላ ውስጥ:የሚሞት:የሚወለድ:የሚያረጅ እና የሚታመም:ገላ ውስጥ:ለምን ተወለድኩ?” ስለዚህ ክርሽና እንዲህ ያስረዳናል:“ይህ የስቃይ ኑሮ የሚቀያየርብን:ይህን የአለማዊ ገላ ይዘን ስለተወለድን ነው:” እነዚያም “ካርሚ” የሆኑት:ማለትም በስሜታዊ ደስታ ግዜያቸውን የሚያጠፉ: ”ካርሚ“ ይባላሉ: ካርሚዎች:ስለ ወደፊት ህይወት ምንም ግድ አይሰጣቸውም:ፍላጎታቸውም: የዚህን ኑሮ የሚያመቻች ነገሮችን ለማግኘት ብቻ ነው: ልክ እንደ ልጅ:ለወላጆቹ ግድ ሳይሰጥ:ሙሉ ቀን ሲጫወት ይኖራል: ለወደፊት ስለአለው ኑሮም ግድ አይሰጠውም:ትምህርትም ለመከታተል ግድ አይሰጠውም: ነገር ግን:በሰው ልጅ ህይወት ላይ እያለን:አዋቂ ሰዎች ከሆንን: ጥረት ማድረግ የሚገባንም:የመሞት:የመወለድ:የማርጀት እና የመታመም ችግር የሌለበትን ህይወት ለማግኘት ነው: ይህም የክርሽና ንቃተ ማህበራችን:ይህንን ለማስተማር ነው የተቋቋመው: አሁን አንዱ እንደዚህ ሊል ይችላል:”ህይወቴን ለክርሽና ንቃት ሰጥቼ ባገለግል“ ”ምን ያህል ለመኖር የሚያስፈልገኝን ነገር ማግኘት እችላለሁ?“ መልሱም በብሃገቨድ ጊታ ተገልጿል:”ማንም ሰው በክርሽና ንቃት በማገልገል ላይ የሚገኝ“ የሚያስፈልገውን ነገር በሙሉ ክርሽና ያቀርብለታል: ክርሽና ለሁሉም የሚያስፈልጋቸውን ነገር በሙሉ እያቀረበ ይገኛል: ”ኤኮ ዮ ባሁናም ቪዳድሃቲ ካማን“ ያም አንድ አምላክ እና ፈጣሪ:ህይወት ላላቸው ሁሉ የሚያስፈልጋቸውን እያቀረበ ይገኛል: ስለዚህም ለክርሽና አገልጋይ:ወደ መጣበት ቤቱ ወደ ፈጣሪ ዘንድ ለመመለስ ለሚያስበው:ምንም እጥረት አይኖርበትም: በብሃገቨድ ጊታ:ክርሽና በእኔ ተማመኑ ብሏል “ቴሻም ሳታታ ዩክታናም ዮጋ ክሴማም ቫሃሚ አሃም” (ብጊ10 10 ) “የእኔ አገልጋይ ሁልግዜ በእኔ አገልግሎት ላይ ይገኛል” “የህይወቱንም አስፈላጊ ነገሮች ሁሉ አቀርብለታለሁ” በተግባር የተሰራም ምሳሌ ለማሳየት ከተፈለገ:በእኛ በክርሽና ንቃተ ማህበር:አሁን ከአንድ መቶ በላይ የሚሆኑ ቅርንጯፎች አሉን: በየእያንዳንዱም ቤተ መቅደስ:ከ25 ያላነሱ እና እስከ 250 የሚሆኑ አገልጋዮች እየኖሩ ይገኛሉ: ቢሆንም ግን የተወሰነ ወርሃዊ ገቢ የለንም: በወርም ከ 80000 ዶላር በላይ:ለቅርንጫፎቻችን እያጠፋን እንገኛለን: ቢሆንም በክርሽና በረከት ምክንያት ምንም የጎደለብን ነገር የለም: ሁሉም ነገር ቀርቦልን ይገኛል: አንዳንድ ግዜ ብዙም ሰው በዚህ ይደነቃል:“እነዚህ ሰዎች ስራ አይሰሩም” “ሙያም አይወስዱም:ሃሬ ክርሽና ሲዘምሩ ብቻ ይገኛሉ: ታድያ እንዴት አድርገው ነው የሚኖሩት?” ብለው ይጠይቃሉ: “ድመቶች እና ውሾች በፈጣሪ ምርቃት ለመኖር የሚችሉ ከሆነ:ይሄ ጥያቄ የማያስፈልግ ነው:” “አገልጋዮች በአምላክ በረከት ተመችቷቸው እና ሁሉ ተሟልቷላቸው ለመኖር ይችላሉ” ይህም ጥያቄ የለውም:ነገር ግን:አንድ ሰው እንዲህ ቢጠይቅ:“የክርሽና ንቃቴን እየተከታተልኩ ነው” “ነገር ግን በብዙ ነገር እየተሰቃየሁ እገኛለሁ” ብሎ ቢያስብ: ለነሱም ሆነ:ለእኛ:መመሪያችን እንዲህ ነው:“ማትራ ስፓርሻስ ቱኩንቴያ:ሺቶሽና ሱክሃ ዱክሃ ዳህ” (ብጊ 2 14) “እነዚህም ስቃይ እና ደስታዎች:ልክ እንደ ክረምት እና በጋ ይቆጠራሉ” በክረምት ቀዝቃዛ ውሃው በጣም የሚያሳምም ነው:በበጋ ደግሞ በጣም ደስ ያሰኛል: ታድያ የውሃ ባህርይ ምንድን ነው?የሚያስደስት ነው ወይንስ የሚያሳምም? የውሃ ባህርይ የሚያሳምም ወይንም የሚያስደስት አይደለም:ነገር ግን እንደ ወቅቱ:ባህርዩው የለያያል: ሲነኩት:እንደ ወቅቱ:ሊያምም ይችላል ወይንም ሊያስደስት ይችላል: እነዚህም የሚፈራረቁ ደስታ እና ስቃይ እዚህ በደንብ ተገልፀዋል:“እንደ ወቅት ይመጣሉ ወይንም ይሄዳሉ:ቋሚ አይደሉም” “አጋማ አፓዪኖ አኒትያህ” ማለት “ይመጣሉ ወይንም ይሄዳሉ:ስለዚህ ቋሚ አይደሉም” ክርሽና ስለዚህም ይመክረናል “ታምስ ቲቲክስቫ ባሃራታ” ትእግስት ማድረግ አለብህ: ነገር ግን ዋናውን የክርሽና ንቃትህን መርሳት የለብህም: ሰለዚህ ለአለማዊ ስቃይ እና ደስታ: ብዙ ግድ አይስጥህ: