AM/Prabhupada 0063 - ታላቅ የምርዳንጋ ከበሮ ተጫዋች መሆን ይገባኛል፡፡

The printable version is no longer supported and may have rendering errors. Please update your browser bookmarks and please use the default browser print function instead.


Arrival Lecture -- Dallas, March 3, 1975

እዚህ የሚከናወነውን ሁኔታ እያየሁኝ:በጣም ተደስቻለሁ: ትምህርት ማለት የክርሽና ንቃት ማለት ነው: ይህ ነው ትምህርት ማለት: ክርሽና ታላቁ ጌታችን መሆኑን ብቻ እንኳን ብናውቅ: እርሱ ታላቅ:ነው:እኛም የእርሱ ታዛዥ ነን:ያለን ሃላፊነት እርሱን ማገልገል ብቻ ነው: እነዚህን ሁለት ቃሎች ብቻ ብንረዳ:ህይወታችን የተሳካ ሊሆን ይችላል: ክርሽናን እንዴት ልንሰግድለት እንደሚገባን:እንዴት ለማስደሰት እንደምንችል:ያህል እንኳን ብንማር: እንዴት ልናለብሰው እንደሚገባን:እንዴት እንደምንመግበው ብንማር: እንዴትስ በጌጣ ጌጥ እና በአበባ እንደምናሸበርቀው:እንዴት እንደምንሰግድለት:ብንማር: እንዴት ስሙን እንደምንዘምር:ሁሉ ብናስብ: ያለ ምንም ሌላ ትምህርት ቤት ሳንገባ:በዚህ ህዋ ውስጥ:እንከን የሌለው ሰው ለመሆን ትችላላችሁ: ይህ የክርሽና ንቃት ነው:ኤ ቢ ሲ ዲ ትምህርት አያስፈልገውም: የሚያስፈልገው:የአእምሮአችንን አስተሳሰብ መቀየር ብቻ ነው: እነዚህም ልጆች ከመጀመሪያው ህይወታቸው መማር ከጀመሩ:ህይወታቸው የቀና ይሆናል: እኛም በልጅነታችን እንደዚህ ለመማር: በወላጆቻችን እድል ተሰጥቶናል: ብዙ መንፈሳዊያን ባህታዊዎች አባታችን ቤት ይመጡ ነበር: አባቴ ቫይሽናቫ ነበረ:እኔንም ቫይሽናቫ እንድሆን ይመኝልኝ ነበረ: አባቴም መነፈሳዊ ሰው ቤታችን በመጣ ቁጥር:እንዲህ ብሎ ይጠይቃቸው ነበር: ”እባካችሁ ልጄ ጥሩ የራድሃራኒ አገልጋይ እንዲሆን መርቁልኝ“ ይላቸው ነበር: ፀሎቱም ይህ ብቻ ነበረ:ለሌላ ነገር ፍጹም አልፀለየም: እንዴት ምርዳንጋ (ከበሮ) መጫወት እንደምችልም አስተምሮኝ ነበር: እናቴ ግን ትቃወመው ነበረ: በዚያን ግዜ ሁለት አስተማሪዎች ነበሩኝ:አንዱ ኤ ቢ ሲ ዲ ለማስተማር ሲሆን ሌላው ደግሞ ምርዳንጋ ለማስተማር ነበር: አንዱ አስተማሪ ምርዳንጋ ሲያስተምረኝ:ሌላው ደግሞ እድሉ እስከሚደርስ ይጠብቅ ነበረ: እናቴም እንዲህ ብላ ትቆጣ ነበረ:”ምንድነው ይሄ?ከበሮ ታስተምረዋለህ?“ ይህን ምርዳንጋ (ከበሮ) ተምሮ ልጁ ምን ሊሆን ነው? ምናላልባትም አባቴ ትልቅ የምርዳንጋ ተጫዋች እንድሆን ፈልጎ ይሆናል:(ሣቅ) እንደዚሁም ሁሉ እኔ የአባቴ ብዙ ውለታ ከፋይ ነኝ: ይህንንም የፃፍኩትን የክርሽና መጽሃፍ በእርሱ ስም አሳትሜዋለሁ: ይህንን ነበረ አባቴ የፈለገው:የብሃገቫታ እና የሽሪማድ ብሃገቨታም ሰባኪ እና አስተማሪ እንድሆን በጣም ይፈልግ ነበረ: የምርዳንጋም ተጫዋች እና የራድሃራኒ አገልጋይ እንድሆን ፍላጎቱ ነበረ: እንደዚሁም ሁሉም ወላጆች እንዲህ ማሰብ አለባቸው: አለበላዛ ግን አባት እና እናት ለመሆን መመኘት አያስፈልግም:ይህም የቅዱስ መፃህፍቶች (ሻስትራ) ትእዛዝ ነው: ይህም በሽሪማድ ብሃገቨታም በ5ኛው ምእራፍ ተጠቅሷል: ”ፒታ ና ሳ ስያት ጃናኒ ና ሳ ስያድ ጉሩር ና ሳ ስያት ስቫ ጃኖ ና ሳ ስያት“ እንዲህም ብሎ ውሳኔው ደግሞ:”ና ሞቻዬድ ያህ ሳሙፔታ ምርትዩም“ አንድ መንፈሳዊ መምህር ተማሪውን ለማዳን ካልቻለ: በድንገት ለሚመጣው ለአደገኛው ሞት:ሊያዘጋጀው ካልቻለ:ጉሩ ወይንም መንፈሳዊ መምህር ሊሆን አይገባውም: አንድ ሰው አባትም ወይንም እናት ለመሆን አይገባውም:ይህም ለሞት ሊያዘጋጇቸው ካልቻሉ ነው: እንዲሁም ጓደኛ፣ ዘመድ:ወይንም አባት መሆን አይገባውም: አንዱ ሰው ሌላውን ከዚህ ከሞት አፋፍ ሊድንበት የሚችለውን ትምህርት ካልቻለ:ዝምድናው ፋይዳ የለውም: ይህም ትምህርት በመላው አለም የተፈለገ ነው: ይህም መንገዱ በጣም ቀላል ነው: አንድ ሰው የክርሽናን ንቃት በማዳበር ብቻ:እስርስር ከሚያደርገው:ትውልድ:ሞት: እርጅና እና ህመም:መገላገል ይችላል: