AM/Prabhupada 0065 - እያንዳንዱ ሰው ደስተኛ ይሆናል፡፡

Revision as of 06:07, 29 November 2017 by Sahadeva (talk | contribs) (Text replacement - "<!-- END NAVIGATION BAR --> <!-- BEGIN ORIGINAL VANIQUOTES PAGE LINK-->" to "<!-- END NAVIGATION BAR --> <!-- BEGIN ORIGINAL VANIQUOTES PAGE LINK-->")
(diff) ← Older revision | Latest revision (diff) | Newer revision → (diff)


Arrival Lecture -- Gainesville, July 29, 1971

እንግዳ: በህብረተሰባችሁ ውስጥ:ለሌላ ሰዎች ቦታ አለ? ይህም ክርሽናን በቀጥታ ባልሆነ መንገድ: ማለትም ቤተ መቅደስ እየኖሩ ሙሉ ቀን ከመዘመሩ ሌላ: ፕራብሁፓዳ:አይደለም:የእኛ መመሪያ እንዲህ ነው:ለምሳሌ ውሃን በዛፉ ስር ላይ ብታጠጡ: ይህ ውሃ በዛፉ ቅጠላ ቅጠል:ግንዶች እና ቅርንጫፎች ሁሉ ይሰራጫል:ዛፉም የለመለመ ሊሆን ይችላል: ነገር ግን ቅጠሉን ብቻ የምታጠጡት ከሆነ ቅጠሉም ይደርቃል:ቅርንጫፎቹም ሁሉ ይደርቃሉ: ምግባችሁን ወደ ሆዳችሁ ከላካችሁት: የሰውነታችሁ ሃይል ወደ ጣቶቻችሁ: ወደ ፀጉራችሁ: ወደ ጥፍራችሁ ሁሉ ይሰራጫል: ምግቡን ግን ወደ ሆድ ሳይሆን እጃችሁ ላይ ብቻ ብታስቀሩት:ምንም ፋይዳ አይኖረውም: ምግቡም ይባክናል: ይህም የበጎ አድራጎት ስራ ሁሉ የክርሽና ንቃት ከሌለው የሚባክን በጎ አድራጎት ይሆናል: በብዙ መንገድ የሰው ልጅ ህብረተሰብን ለመርዳት እየሞከሩ ነው: ነገር ግን ሁልግዜ ፋይዳ ቢስ እይሆነ እና በውጤቱ አለመደሰት አለ: ይህም የክርሽና ንቃት ስለሞሚጎለው ነው: ሰዎች እንዴት የክርሽና ንቃትን እንደሚያዳብሩ ከተማሩ:ሁሉም ሰው ደስተኛ ይሆን ነበረ: ስለዚህም ይህን ህብረተሰብ የሚገባ:የሚያዳምጥ:የሚተባበር ሁሉ ደስተኛ ይሆናል: ስለዚህ የእኛ መመሪያ የተፈጥሮ መመሪያ ነው: አምላክን መውደድ:አምላክንም የመውደድ ችሎታችን የዳበረ ከሆነ:በተፈጥሮአችን ሁሉንም ሰው መውደድ እንችላለን: ልክ እንደ ንቃት ያለው ሰው:አምላክን ስለሚያፈቅር:እንስሶችንም ያፈቅራል: ወፎችንም:አውሬዎችንም:ሁሉንም ይወዳል: ግን እነዚህ በጎ አድራጊ ነኝ የሚሉ ግን: ለሰው ልጅ ፍቅር እያሳዩ: እንስሳዎችን ግን ይገሏቸዋል: ታድያ ለምንድን ነው እንስሳዎቹን የማይወዷቸው?ምክንያቱም የበጎ አድራጎት እንከን ስለአላቸው ነው: ነገር ግን የክርሽና ንቃት ያለው ሰው:እንሰሳ ከመግደል ፈጽሞ ይወገዳል:ለእንስሳዎችም ችግር አይፈጥሩባቸውም: ይህም የዩኒቨርሳዊ ፍቅር ነው: ወንድምህን እና እህትህን ብቻ የምታፈቅር ከሆነ:ይህ የዩኒቨርሳዊ ፍቅር አይደለም: ዩኒቨርሳል ፍቅር ማለት:ሁሉንም ማፍቀር ማለት ነው: ይህም የዩኒቨርሳል ፍቅር የሚመሰረተው:የክርሽናን ንቃት በማዳበር ነው:በሌላ መንገድ ሊሆን አይችልም: ሴት እንግዳ:እንደሰማሁት ከሆነ አንዳንድ ድቮቲዎች (አገልጋዮች) ከቤተሰቦቻቸው ተለያይተዋል: ይህም ከወላጆቻቸው ጋር ስለሆነ:ይህም በቤተሰቡ ቅሬታ ፈጥሯል: ምክንያቱም ቤተሰቦቻቸው ይህንን ሊረዱት አይችሉም: ስለዚህ አንተ ይህን እንዲቀልላቸው ምን ልትላቸው ትችላለህ? ፕራብሁፓዳ: በክርሽና ንቃት ያለ ልጅ: ለቤተሰቡ:ለወላጆቹ:ለአገሩ ሰው:ለህብረተሰቡ:ትልቅ አስተዋጽኦ እያደረገ ነው: ክርሽና ንቃትስ ባይከተሉ:ምን አይነት ስራ ነበር ለወላጆቻቸው የሚሰሩት? ብዙዎቹም የተለያዩ ነበሩ: ነገር ግን: ልክ ፕራላድ ማሃራጅ ትለቅ ድቮቲ እንደነበረው ሁሉ አባቱ ደግሞ ድቮቲ ያልሆነ ነበር: አልፎ ተርፎም አባቱ በነርሺንጋዴቫ ተገደለ: ነገርግን ፕራህላድ የሚፈለገውን ምርቃት እንዲያገኝ ሲጠየቅ: እኔ ነጋዴ አይደለሁም:የእኔ ጌታ: እኔ በፍቅር ለአደረግሁት ስራ:ክፍያ አያስፈልገኝም: ይቅርታ ይደረግልኝእና: ንርሺምሃም በጣም ተደሰተ:“ይህ ነው ንጹህ ድቮቲ ማለት” ነገር ግን ይህም ንጹህ ድቮቲ ጌታውን እንዲህ ብሎ ጠየቀው: ጌታዬ ሆይ:አባቴ በአማላክ የማያምን ነበር:ብዙ ሃጥያትም ፈጽሞ ነበር: እኔ የምለንምህ ነገር ቢኖር:አባቴ ከእንዚህ ሃጥያቶች ሁሉ ነፃ እንዲወጣ ነበር: ንርሺማዴቫም እንዲህ አለ:“ለአባትህ አንተ ልጁ ስለሆንክ:አባትህ ወዲያውኑ ነጻ ወጥቷል” ”ብዙ ሃጥያትም ይፈጽም እንጂ:አንተ ልጁ ስለሆንክ እሱ ነጻ ወጥቷል“ አባትህም ብቻ ሳይሆን:የአባትህም አባት እንዲሁም እስከ ሰባት ትውልድ ድረስ ሁሉም ነፃ ወጥተዋል: እንደዚሁም ሁሉ አንድ ቫይሽናቫ በቤቱ ካለ:ከሃጥያት ነፃ የሚያወጣው አባቱን ብቻ ሳይሆን:አያቱንም ቅድም አያቱንም ወዘተ ነው: ይህ ነው በጣም ጥሩ የሆነው የቤተሰብ አገልግሎት: በነገራችን ላይ ይህ ለአንዱ ተማሪዬ ተከስቶ ነበር:“ካርቲኬያ” እናቱም የእኛን ህብረተሰብ ትወድ ነበር:አንዳንድ ግዜም እናቱን ለማየት ሲፈልግ: እናቱም “አንተ እዚህ ቁጭ በል እኔ የዳንስ ፓርቲ አለብኝ” ትለው ነበረ: ይህም ልጅ የክርሽና ንቃት ስለአለው: ለእናቱ ስለክርሽና ብዙውን ግዜ ያጫውታት ነበር: በሞት ደረጃም ላይ እያለች:ልጁን እንዲህ ብላ ጠየቀችው:“ያንተ ክርሽና የት አለ? ይኅውና!” ከዚያም ወዲያውኑ ሞተች: ይህም ማለት በሞት አፋፍ ላይ እያለች:ክርሽናን ለማስታወስ በቃች ማለት ነው:በዚህም ምክንያት ወዲያውኑ ከዚህ አለም ነጻ ለመውጣት ቻለች: ይህም በብሃገቨድ ጊታ ተገልጿል:“ያም ያም ቫፒ ስማራን ሎኬ ትያጃትዪ አንቴ ካሌቫራም (ብጊ 8 6 ) በሞት አፋፍ ያለ ሰው:ክርሽናን ለማስታወስ ከቻለ:ህይወቱ የተሳካ ሊሆን ይችላል: ታድያ ይህችም እናት:የክርሽና ንቃት ያለው ልጅ ስለአላት:ነፃ ወጣች: እንደዚሁም ሁሉ:ወደ ክርሽና ንቃተ ባህር እንኳን ሳትመጣ:ነጻነትዋን አገኘች: ስለዚህም ይህ ነው ጥቅሙ: