AM/Prabhupada 0079 - ምንም አይነት ክፍያ ለእኔ አያስፈልግም፡፡

The printable version is no longer supported and may have rendering errors. Please update your browser bookmarks and please use the default browser print function instead.


Lecture on SB 1.7.6 -- Hyderabad, August 18, 1976

እነዚህ የውጭ አገር ሰዎች:ሂንዱ አይደሉም:ወይንም ህንዳውያን አይደሉም ወይንም ብራህማናዎች አይደሉም: እንዴት ነው ይህንን መንፈሳዊ ንቃት የወሰዱት?ሞኞች እና ተንኮለኞችም አይደሉም: የመጡትም ከተከበረ እና ከተማሩ ቤተሰቦች ነው: አሁን ኢራን ውስጥም ቅርንጫፎች አቋቋቁመናል:በቴህራን ውስጥ:ከዚያ ነው አሁንም የመጣሁት: ከሞሃመዳን ቤተሰቦችም የመጡ ብዙ ተማሪዎች አሉን:እነርሱም እየተከተሉ ነው: አፍሪካዊያንም እየተከተሉ ነው:አውስትራሊያዎችም እየተከተሉ ነው: በአለም ዙርያ ሁሉ:ይህ ነው የጌታ ቼይታንያ ሚሽን: “ፕሪትሂቪቴ አቼ ያታ ናጋራዲ ግራም ሳርቫትራ ፕራቻራ ሃይቤ ሞራ ናም” ይህ ይጌታ ቼይታንያ ትንቢት ነው: በአለም ላይ በሚገኙ:በእያንዳንዱ ከተማ እና መንደር: ይህ የክርሽና ንቃት እንቅስቃሴ:ይሰራጫል: ስለዚህ ለእኔ ነጥብ የለኝም:ይህ የእኔ ትንሿ መዋጮ እና በትህትና የቀረበች ናት: ስለዚህ አንድ ሰው ይህን የሚያስፈፅም ከሆነ:ለምን ሁላችንም እንዲህ አናደርግም? ቼይታንያ ማሃፕራብሁ:ስልጣን እና ሃይል ለሁሉም ህንዳውያን ሰጥቷል: ብሃረታ ብሁሚቴ ሆይላ ማኑስያ ጃንማ ያራ (ቼቻ አዲ 9.41) እርሱም የተናገረው ለሰው ዘር እንጂ ለድመቶች እና ለውሾች አይደለም: “ማኑሻ ጃንማ ያራ ጃንማ ሳርትሃካ ካሪ” በመጀመሪያ:የህይወታችን አላማ ምን እንደሆነ መረዳት ያስፈልጋል: ይህም እንዲህ ይባላል “ጃንማ ሳርትሃካ:ጃናማ ሳርትሃካ ካሪ ካራ ፓራ ኡፓካራ” ስለዚህ ሁሉም ቦታ ሂዱ: ይህም የክርሽና ንቃት በጣም የሚፈለግበት ደረጃ ላይ ነው ያለው: