AM/Prabhupada 0101 - ጤነኛው ሕይወታችን ዘለዓለማዊውን የደስታ ሕይወትን ማግኘት ማለት ነው፡፡

The printable version is no longer supported and may have rendering errors. Please update your browser bookmarks and please use the default browser print function instead.


Press Conference -- April 18, 1974, Hyderabad

እንግዳ 2:የክርሽና ንቃት የመድረሻ አላማው ምንድን ነው?

ፕራብሁፓዳ:የመድረሻ አላማው አይደለም:ለማለትም እምፈልገው:የመድረሻ አላማው:እንደምናውቀው በአለም ላይ: የመንፈስ እና የአለማዊ ንጥረ ነገሮች አሉ: ምድራዊ አለም እንደአለም ሁሉ መንፈሳዊ አለምም አለ: ”ፓራስ ታስማት ቱ ብሃቫህ አንያህ አቭያክታህ አቭያክታት ሳናታናሃ (ብጊ 8.20) መንፈሳዊ አለም: ዘለአለማዊ ነው:ይህ ምድራዊ አለም ደግሞ: ግዜያዊ ነው: እኛ ደግሞ መንፈሳዊ ነፍስ ነን:ዘለአለማዊም ነን: ስለዚህ የእኛ ጥረት ሁሉ ወደ መንፈሳዊ አለም ለመመለስ ነው: በዚህ አለም ላይ ቀርተን:ገላችንን ከመጥፎ መጥፎ ወይንም ወደ ጥሩ አለማዊ ገላ እየለዋወጡ ለመኖር: ምንም ምኞት የለንም: ይህ ነው የእኛ ስራ:ይህ አለም ህመማችን ነው: የእኛ ጤነኛ ህይወት የዘላለማዊ ኑሮን ስንደሰት ነው: “ያድ ጋትቫ ና ኒቫርታንቴ ታድ ድሃማ ፓራማም ማማ” (ብጊ 15.6) አያችሁ?ይህ የሰው ህይወታችንንም:ይህን ብቁ የሆነ ደረጃን ለማግኘትን: ጥረት ለማድረግ እንድንጠቀምበት ያስፈልጋል: ለሚለዋወጥ ነገር: ሌላ አለማዊ ገላ ይዘን እንድንወለድም ጥረት ማድረግ አይገባንም:ይህ ነው የህይወታችን አላማ:

እንግዳ 3:ይህ ለመንፈሳዊነት ብቁ መሆን: በአንድ የሰው እድሜ ይቻላልን?

ፕራብሁፓዳ:አዎን እንዲያውም በአንድ አፍታ ወይንም ቅፅበት ይቻላል:ይህም ከተስማማችሁ ነው: ክርሽና እንዲህ ብሏል:“ሳርቫ ድሃርማን ፓሪትያጅያ ማም ኤካም ሻራናም ቭራጃ አሃም ትቫም ሳርቫ ፓፔብህዮ ሞክሺያዪሽያሚ ማ ሹቻሃ” (ብጊ 18.66) በዚህ አለም ገላችንን የምንቀያይረው:በሀጥያታዊ ተግባራችን ነው: ነገር ግን ለክርሽና ሙሉ ልቦናችንን ከሰጠን እና የክርሽና ንቃትን ከወሰድን:በአንድ አፍታ ወይንም በቅፅበት ወድ መንፈሳዊ መድረክ መስፈር እንችላለን: “ማም ቻዮ ቭያብሂቻሬና ብሃክቲ ዮጌና ሴቫቴ ሳጉናን ሳማቲያይታን ብራህማ ብሁያያ ካልፓቴ” (ብጊ 14.26) ልክ ንጹህ የሆነ ድቮቲ ደረጃ ላይ እንደደረሳችሁ:ይህን የአለማዊ ጉጉቶችን በቀላሉ ለማለፍ ትችላላችሁ: “ብራህማ ብሁያያ ካልፓቴ” በመንፈሳዊ መድረክም ላይ ትሰፍራላችሁ: በዚህም በመንፈሳዊ መድረክ ላይ ህይወታችሁን ብታልፉ:በቀጥታ ወደ መንፈሳዊ አለም ትሄዳላችሁ: