AM/Prabhupada 0106 - የትሁት አገልግሎትን ሊፍት በመጠቀም ወደ ክርሽና በቀጥታ ሂዱ፡፡

The printable version is no longer supported and may have rendering errors. Please update your browser bookmarks and please use the default browser print function instead.


Lecture on BG 18.67 -- Ahmedabad, December 10, 1972

“ማማ ቫርትማኑ ቫርታንቴ” ማለት: ለምሳሌ:በአሜሪካ ውስጥ ብዙ ረጃጅም ህንፃዎች ይገኛሉ: በቅርብ ግዜ የሰማነውም:105 ፎቅ ነው: ወደ ከፍተኛው ፎቅ ለመሄድም ደረጃ ይኖራል: ለምሳሌ ሁሉም ሰው ደረጃ ለመውጣት እየሞከረ ነው እንበል:አንዳንዶቹ 10 ደረጃ አልፈዋል እንበል: ሌሎች 50 ደረጃ እንዲሁም ሌሎች 100 ደረጃ:አልፈዋል እንበል: 200 ደረጃም መጨረስ አለባቸው እንበል: ደረጃዎቹ ተመሳሳይ ናቸው:“ማማ ቫርትማኑ ቫርታንቴ” አላማውም ወደ ከፍተኛው ፎቅ ለመድረስ ነው: እንዲሁም 10 ደረጃ የወጣው ሰው:50 ደረጃ ከወጣው ዝቅተኛ ነው: 50 ደረጃ የወጣው ደግሞ:100 ደረጃ ከወጣው ዝቅተኛ ነው: ቢሆንም እንኳን:የተለያዩ የዓላማ ሥርአቶች አሉ:ሁሉም የዓላማ ሥርአቶች አንድ አይደሉም: መንፈሰ ንቁ የሆኑ ሁሉ:አምላክን ለመቅረብ አላማቸው አንድ ነው:ይህም በሥርአተ ካርማ:ግናና:ዮጋ:ብሃክቲ:ለመቅረብ ነው:ነገር ግን ከፍተኛው ሥርአት “ብሃክቲ” ነው:(አምላክን በፍቅር ማገልገል) የብሃክቲም መድረክ ላይ ስትወጡ:ክርሽናን ለመረዳት ትችላላችሁ: በካርማ:በግያና:በዮጋ ሳይሆን: ትሞክራላችሁ:ወደ መድረሻችሁም ለመድረስ ትሞክራላችሁ: ክርሽና ግን እንዲህ አለ:“ብሃክትያ ማም አብሂጃናቲ (ብጊ18 55)(በብሃክቲ ብቻ) በግያና:በካርማ:በዮጋ:አይለንም: በዚህ መንገድ ወይንም ሥርአት ክርሽናን ልትረዱት አትችሉም ወይንም ወደ ፊት ልትራመዱ አትችሉም: ክርሽናን ለመረዳት ከፈለጋችሁ ግን:በብሃክቲ ነው: ”ብሃክትያ ማም አብሂጃናቲ ያቫን ያሽ ቻስሚ ታትቫታሃ“ (ብጊ18 55) ይህ ነው ስርአቱ:ስለዚህ እንዲህ ተብሏል:”ማማ ቫርትማኑ ቫርታንቴ“ ክርሽናም እንዲህ አለ: "ሁሉም ወደ እኔ:እንደ አቅሙ እና እንደ ችሎታው ለመምጣት ይሞክራል“ ”ነገርግን እኔን በትክክል ሊረዳኝ የሚፈልግ:የቀላሉን የብሃክቲን ሥርአት ይከተላል“ ልክ እንደ ደረጃው:በአሜሪካ እና በዩሮፕ: በጎን እና በጎን ሊፍት እና ደረጃዎችን እናገኛለን: ደረጃውንም ላይ ድረስ ከመውሰድ:ሊፍቱን መውሰድ ትችላላችሁ: እንደዚሁም በቶሎ መድረስ ትችላላችሁ: እንደዚሁም የብሃክቲን ሊፍት ብትወስዱ:ወዲያውኑ ከክርሽና ጋር መገናኘት ትችላላችሁ: ደረጃ በደረጃ ከመሄድ ማለት ነው:ለምን ብላችሁ? ስለዚህ ክርሽና እንዲህ ይላል:”ሳርቫ ድሃርማን ፓሪትያጅያ ማም ኤካም ሻራናም ቭራጃ“ (ብጊ18 66) ”ለእኔ ብቻ ሙሉ ልቦናችሁን ስጡኝ እና ሌላውን ሃላፊነታችሁን እኔ እጨርስላችኋለሁ“ ለምን ብላችሁ ደረጃ በደረጃ መታገል አለባችሁ?