AM/Prabhupada 0110 - የቀድሞዎቹ አቻርያ መምህሮች አሻንጉሊት ሁኑ፡፡

The printable version is no longer supported and may have rendering errors. Please update your browser bookmarks and please use the default browser print function instead.


Morning Walk -- April 19, 1973, Los Angeles

ስቫሩፕ ዳሞዳር:ሽሪማድ ብሃገቨታምን ቢሰሙ:ልቦናቸው ሊቀየር ይችላል:

ፕራብሁፓድ:በእርግጥ:ትላንትና አንዱ: ተማሪዎቻችንን አመስግኖ ነበር: “ይህንን ብሃገቨታም ስለምታቀርቡልን በጣም ለምስጋና ተገደናል” አንዱ እንደዚህ አላለምን? ድቮቲ:አዎን:ትሪፑራሪ እንዲህ ብሎ ነበር:

ፕራብሁፓድ:አዎን ትሪፑራሪ:እንደዛ ብሎ ነበርን? ትሪፑራሪ:አዎን:ሁለት ልጆች አይሮፕላን ማረፊያ:ሁለት ጥንድ የሽሪማድ ብሃገቨታም መጽሃፍቶች ገዝተው ነበረ: ጃያቲርትሃ:ሙሉውን ጥንድ?ስድስት ቮሉዩም: ብሃገቨታሙንም ይዘው በጣም እናመሰግናለን አሉ: ከዚያም ወደ ሎከራቸው ውስጥ:አስቀመጥዋቸው እና:አይሮፓላናቸውን እየጠበቁ እያሉ:በእጃቸው የመጀመሪያውን ካንቶ ያዙ: ፕራብሁፓዳ:አዎን:ማንም ታማኝ እና ትሁት ጥረት ያለው ሰው ለዚህ ለእንቅስቃሴያችን ለምስጋና ይገደዳሉ: እነዚህንም መፃህፍቶች በማከፋፈላችሁ:ለክርሽና ትልቅ አገልግሎት እያበረከታችሁ ነው: ለሁላችንም ክርሽና እንዲህ ብሎናል:“ሳርቫ ድሃርማን ፓሪትያጅሃ ማም ኤካም ሻራናም ቭራጃ” (ብጊ 18 66) ስለዚህ ማነም ይህንን አገልግሎት የሚሰጥ ሰው: “ልቦናውን የሰጠ ሰው” በክርሽና በደንብ አድርጎ የታወቀ ይሆናል: ይህም በብሃገቨድ ጊታ ተጠቅሷል:“ናቻ ታስማን ማኑሽዬሹ (ብጊ 18 69) በሰው ልጅ ህብረተሰብ ውስጥ:ክርሽናን ለማስተማር ከሚያግዘው ሰው በላይ ማንም:ውድ አይሆነውም: ሃሬ ክርሽና: ብራህማናንዳ:እኛ የእናንተ አሻንጉሊት ነን:ሽሪላ

ፕራብሁፓድ:መጽሃፍቶቹን የሰጠህን አንተው ነህ:

ፕራብሁፓድ:አይደለም: እኛ ሁላችንም የክርሽና አሻንጉሊቶች ነን:እኔ ራሴ አሻንጉሊት ነኝ: አሻንጉሊት:ይህ ሲወርድ ሲዋረድ ተያይዞ የመጣ ነው:ሁላችንም አሻንጉሊቶች መሆን አለብን: እኔም የጉሩ ማሀራጄ አሻንጉሊት እንደሆንኩኝ ሁሉ:እናንተም እንደዚሁ ብትሆኑ:ወደፊት መራመድ ትችላላችሁ: የኛ ኑሮ ማሳካት የሚመጣው:ያለፉት መሪዎቻችን አሻንጉሊት ስንሆን ነው: “ታንዴራ ቻራና ሴቪ ባሃክታ ሳኔ ቫስ” በድቮቲዎች ክበብ መሃከል መኖር እና: የቀድሞ አርአያዊ መምህሮቻችን አሻንጉሊት መሆን ነው: ይህ ውጤታማ ያደርገናል:ስለዚህ ይህን ለማድረግ ጥረት ላይ ነን: የክርሽና ንቃተ ማህበረተኛ መሆን እና የቀድሞ መሪዎቻችንን ማገልገል:ይኅው ነው: “ሃሬር ናማ ሃሬር ናማ” (ቼቻ አዲ 17 21) ህብረተሰቡ ወደ እኛ ይመጣል:የእኛንም ትምህርት ያመሰግኑታል:ነገር ግን ጊዜ ይወስዳል: ስቫሩፕ ዳሞዳር:በአሁኑ ግዜ ከሁለት አመቱ በፊት በላይ:እያመሰገኑት ነው ያለው:

ፕራብሁፓድ:አዎን: ስቫሩፓ ዳሞዳር:አሁን ትክክለኛ ፍልስፍና መረዳት ጀምረዋል: