AM/Prabhupada 0119 - መንፈሳዊው ነፍስ ሁሌ እንደ አረንጓዴ ነው፡፡

The printable version is no longer supported and may have rendering errors. Please update your browser bookmarks and please use the default browser print function instead.


Lecture on BG 2.1-10 and Talk -- Los Angeles, November 25, 1968

ፕራብሁፓድ:አዎን:

ሽሪማቲ:እድሜ ማለት እርሱ ይሆን?ነፍስ ከገላ ስትወጣ ይህስ እርጅና ማለት ነውን?

ፕራብሁፓድ:አይደለም:ነፍስ አረጀች ማለት አይደለም:ገላችን እየተቀያየረ ነው:ያ ነው ሂደቱ: ይህም ተገልጿል: “ዴሂኖ ስሚን ያትሃ ዴሄ:ኮማራም ዮቫናም ጃራ:ታትሃ ደሃንታራ ፕራፕቲር ድሂራስ ታትራ ና ሙህያቲ” (ብጊ 2 13) ነፍስ ሁልግዜ ለዘለአለም የማታረጅ ለምለም ናት:ገላ ግን ሁልግዜ ይቀያየራል: ይህን መገንዘብ አለባችሁ:ገላ ሁልግዜ እንደተቀያየረ ነው:ይህን ሁሉም ይረዳል: በልጅነታችሁ እንደምታውቁት ገላችሁ ልዩ ነበር: ልክ እንደ እዚች ህጻን:የተለየ ገላ ነበር: ይህች ህጻን ደግሞ:ወጣት ልጅአገረድ ስትሆን የተለየ ገላ ትይዛለች: ነገር ግን:ነፍስ በዚህኛውም ሆነ በዚያኛውም ገላ ነበረች: ይህ ነው ማስረጃው:ነፍስ አትቀያየርም:ነገር ግን ገላችን ሁሌ እንደተቀያየረ ነው: ይህ ነው መረጃው:እኔ ስለ ልጅነቴ አስብ ይሆናል: ይህም ማለት ያ ስለልጅነት የማስበው ገላ:የእኔው የእራሴ ገላ ነበር: በልጅነቴ የማደርገውን ነገር ሁሉ አስታውሳለሁ:ይህንንም ያንንም ሳደርግ: ነገር ግን ያ የልጅነት ገላ ሂዷል: ይህም ማለት የልጅነት ገላዬ ተቀይሯል: እኔ ግን እስከ አሁን አለሁ አልተቀየርኩም:ይህ ነው መደምደሚያው: ይህ አይደለምን? ይህ ቀላል እውነት ነው: ገላው በተቀየረ ግዜ ሁሉ እኔ አልቀየርም: ሌላ ገላ ውስጥም እገባ ይሆናል:ይህ እኔን ሊለውጠኝም አይችልም: “ታትሃ ዴሃንታራ ፕራፕቲር ድሂራስ ታትራ ና ሙህያቲ” (ብጊ 2 13) ልክ ገላዬን አሁን እንደምቀያይረው ሁሉ: እንደዚሁም ሁሉ በመጨረሻ በሞት ግዜም ሲቀየር:እኔ ሞትኩኝ ማለት አይደለም: ሌላ ገላ ውስጥ እገባለሁ እንጂ:ይህም ተገልጿል:“ቫሳምሲ ጂርናኒ ያትሃ (ብጊ 2 22) ለምሳሌ ሳንያሲ (ባህታዊ)ከመሆኔ በፊት:እንደ ጀንትል ሰው ልብስ እለብስ ነበረ: አሁን ግን ልብሴ የተለየ ነው:ይህም ማለት ሞትኩኝ ማለት አይደለም: አይደለም:ገላዬን መቀየር:ልብሴን እንደቀየርኩት ማለት ነው: