AM/Prabhupada 0126 - ይህም ለመንፈሳዊ አባቴ ደስታ ብዬ የማደርገው ነው፡፡

The printable version is no longer supported and may have rendering errors. Please update your browser bookmarks and please use the default browser print function instead.


Lecture on BG 4.18 -- Delhi, November 3, 1973

ሴት ድቮቲ:እንዲህ ብለህ ነበር :“አንድ ሰራ ለክርሽና ስንሰራ” “ይህ ስራ ክራሽናን እንደሚያስደስት መሞከር አለበት ብለህናል:ይህ ሙከራ ምንድን?”

ፕራብሁፓድ:የመንፈሳዊ አባት ከተደሰተ:ክርሽና ተደሰተ ማለት ነው:ይህንንም በቀን በቀን ትዘምራላችሁ: “ያስያ ፕራሳዶ ብሃጋቫት ፕራሳዶ ያስያፕራሳዳ ና ጋቲ ኩቶ ፒ” የመንፈሳዊ አባት ከተደሰተ:ክርሽናም ተደሰተ ማለት ነው:ይህ ነው ሙከራው: እርሱም ካልተደሰተ ግን:ሌላ ምርጫ የለውም:ይህም ለመረዳት አያዳግትም: ለምሳሌ በቢሮ ውስጥ የሚሰራ ሰው:ሃላፊው ዋና ክሌርኩ:ወይንም ሱፐር ኢንቴንደንቱ ወይንም የክፍሉ ሃላፊ ነው: ሁሉም እየሰሩ:ሱፐር ኢንቴንደንቱ ከተደሰተ: ወይንም ዋና ክሌርኩ ከተደሰተ:አስተዳዳሪ ዳይሬክተሩም ይደሰታል ማለት ነው: ይህም ለመረዳት አስቸጋሪ አይደለም:ለእናንተም ሃላፊያችሁ:የክርሽና ተወካይ መደሰት አለበት: “ያስያ ፕራሳዳ ብሃጋቫት ፕራሳዶ ያስያ” ስለዚህ በመንፈሳዊ አባት መመራት ያሰፈልጋል: ክርሽና እንደ መንፈሳዊ አባት መመሪያ ሁኖ ይመጣል:ይህም በቼይታንያ ቻሪታምሪታ ተጠቅሷል: “ጉሩ ክርሽና ክሪፓያ:ጉሩ ክርሽና ክሪፓያ” ስለዚህ ”ጉሩ ክርፓ“ የጉሩ ምርቃት የክርሽና ምርቃት ነው: እንደዚሁም ሁሉ ሁለቱም በደስታ ከረኩ:መንገዳችንም ግልጽ ነው ማለት ነው: “ጉሩ ክርሽና ክርፓያ ፓያ ብሃክቲ ላታ ቢጅ” (ቼቻ ማድህያ 19 151) እንዲህም ከሆነ የክርሽና አገልግሎታችን የተሳካ ይሆናል: ይህንን ጥቅስ በ “ጉሩ ቫስታካ” መዝሙር አላስተዋላችሁትምን? “ያስያ ፕራሳዳ ብሃጋቫት ፕራሳዶ ያስያፕራሳዳን ና ጋቲህ ኩቶ ፒ” ልክ እንደዚህ እንቅስቃሴያችን:ይህ እንቅስቃሴ የተጀመረው:የእኔን መንፈሳዊ አባት ለማስደሰት ነው: እርሱም እና ቼይታንያ ማሃፕራብሁ:ይህ እንቅስቃሴ በአለም ላይ እንዲስፋፋ ተመኝተው ነበር: ስለዚህም ብዙዎቹን የእኔን መንፈሳዊ ወንድሞች:አዘዛቸው እና ትምህርቱን እንዲያስፋፉ ተመኘ: አንዳንዶቹንም የመንፈስ ወንድሞቼን ወደ ውጭ አገር እንዲያስተምሩ ተልከው ነበር: ነገር ግን በተለያየ ምክንያት ስለአልተሳካላቸው:ተመልሰው ወደ አገር ተመልሰው መጡ: ስለዚህም እኔ ”በዚህ በእርጅና ግዜዬም ልሞክር“ ብዬ አሰብኩኝ የነበረኝም ፍላጎት:የመንፈሳዊ አባቴን:ምኞት ለሟሟላት ብቻ ነበር: እናንተም እያገዛችሁኝ ነው:አሁን ታድያ ውጤቱ እያማረልን ነው: ይህም “ያስያ ፕራሳዳ ብሃጋቫት ፕራሳዳ” ነው: በትጋት እና በሙሉ ልቦና:በመንፈሳዊ አባታችን ተመርተን: አገልግሎታችንን ከሰጠን: ይህ የክርሽናን መደሰት ያመጣል:ክርሽናም ወደ ፊት እንድንገፋ ይረዳናል: