AM/Prabhupada 0156 - ላስተምራችሁ ጥረት የማደርገው የረሳችሁትን ነው፡፡

The printable version is no longer supported and may have rendering errors. Please update your browser bookmarks and please use the default browser print function instead.


Arrival Address -- London, September 11, 1969

ጋዜጠኛ:ለማስተማር የምትሞክረው ትምህርት ምንድን ነው?

ፕራብሁፓዳ:እኔ ለማስተማር የምሞክረው:እናንተ የረሳችሁትን ትምህርት ነው:

ድቮቲዎች:ሀሪ ቦል!ሀሬ ክርሽና!(ሳቅ)

ጋዜጠኛ:የትኛውን:ማለትህ ነው?

ፕራብሁፓድ:ይህም ፈጣሪን ነው: አንዳንዶቻችሁ ፈጣሪ የለም ትላላችሁ:አንዳንዶቻችሁ ደግሞ ፈጣሪ ሞቷል ትላላችሁ: አንዳንዶቻችሁ ደግሞ ፈጣሪ ሰብአዊ ባህርይ የለውም ትላላችሁ:ወይንም ባዶ ነው ትላላችሁ: ይህ ሁሉ ስሜት የማይሰጥ ነው: ስለዚህ እነዚህን ስሜት የማይሰጡ ሰዎች ሁሉ:ፈጣሪ እንደ አለ:ለማስተማር ነው የመጣሁት:ይህ ነው የእኔ ሚሽን: ማንም ስሜት የማይሰጥ ሰው ወደ እኔ መምጣት ይችላል:እኔም ፈጣሪ እንደ አለ ማስረጃ አቀርብለታለሁ: ይህ ነው የእኛ የክርሽና ንቃት እንቅስቃሴ: ይህም ፈጣሪ የማያምኑ:ህብረተሰቦችን መቋቋም ነው: ፈጣሪ አለ:እዚህ ፊት ለፊት እንደምንትየያይም ሁሉ:ከፈጣሪ ጋር ፊት ለፊት ለመተያየት እንችላለን: ታታሪ እና ኮስተር ብላችሁ መንፈሳዊ ኑሮ የምትከታተሉ ከሆነ:ፈጣሪን ማየት ይቻላል: ነገር ግን:ፈጣሪን ለመርሳት እየሞከርን ነው:ስለዚህም ብዙ ስቃይ ላይ እየወደቅን እንገኛለን: ስለዚህ እኔም የማስተምረው:ክርሽና ንቃትን ወስዳችሁ:ደስተኛ እንድትሆኑ ብቻ ነው: በዚህ ስሜት በማይሰጥ:የማያ ማእበል:ወይንም ምትሃት:ተጎትትችሁ አትወሰዱ: ይህ ነው የእኔ መጠይቅ:

ድቮቲዎች:ሀሪ ቦል!