AM/Prabhupada 0162 - የብሀገቨድ ጊታን መልእክት በልቦናችሁ አሳድሩ፡፡

The printable version is no longer supported and may have rendering errors. Please update your browser bookmarks and please use the default browser print function instead.


Press Interview -- October 16, 1976, Chandigarh

በህንድ አገር ውስጥ:ብዙ ስለ ነፍስ ስራ የሚያስተምሩ የቬዲክ መፃህፍቶች አሉ: በሰው ልጅ ትውልድ ደግሞ:ስለ መንፈሳዊ ህይወታችን ፍላጎት ካላደረብን:ልክ ራስን እንደመግደል ይቆጠራል: በህንድ አገርም ተወልደው የነበሩ ታላላቅ አስተማሪዎችም መልእክት ይኅው ነበር: በቅርብ የነበሩ አቻርያዎች (በአርአያ የሚያስተምሩ) ከዚህ ቀደም:ብዙ ታላላቅ አቻርያዎች ነበሩ:እንደ እነ ቭያሳዴቭ እና ሌሎች: ዴቫላ እና ሌላ ብዙ አቻርያዎች: ባለፉት 1500 አመታትም ብዙ አቻርያዎች ነበሩ: እንደነ ራማኑጃ:ማድሃቨ አቻርያ:ቪሽኑስዋሚ: በ500 አመታት ውስጥ ደግሞ:እንደ ጌታ ቼይታንያ ማሃፕራብሁ: እነዚህ ሁሉ ብዙ መንፈሳዊ መጻህፍትን ትተውልን ሂደዋል: በአሁኑ ግዜ ግን ይህ መንፈሳዊ እውቀት ተዘንግቷል: ስለዚህም ጌታ ቼይታንያ ማሃ ፕራብሁ:መልእክቱን ለመላው አለም አስተላልፏል: ሁላችሁም ጉሩ ወይንም መንፈሳዊ መምህር ሁኑ: ታድያ እንዴት ነው ሁሉም መንፈሳዊ መምህር ለመሆን የሚችለው? የመንፈሳዊ አባት መሆን ቀላል ስራ አይደለም: አንድ ሰው የተማረ ወይንም ስለመንፈሳዊ እውቀት ምሁር መሆን አለበት:ሰለ ነፍስ እና ሁሉ የተያያዘውን ነገር መረዳት አለበት ነገርግን ቼይታንያ ማሃፕራብሁ ትንሽ ፎርሙላ ሰጥቶናል: ብሃገቨድ ጊታን በትክክል ከተከተልን:መልእክቱንም ከሰበክን:ያኔ ጉሩ ሆንን ማለት ነው: በቤንጋል ለዚህ የተሰጠው ቃል:“ያሬ ዴክሃ:ታሬ ካሃ: ክርሽና ኡፓዴሽ” (ቼቻ 7 128) ጉሩ መሆን አስቸጋሪ ነው:ነገር ግን የብሃገቨድ ጊታን መልእክት ከሰበካችሁ: እና ያገኛችሁትን ሰው ለማስረዳት ከቻላችሁ: ጉሩ ሆናችሁ ማለት ነው: ስለዚህ ይህ የክርሽና ንቃት ማህበር:የተቋቋመው ለዚሁ አላማ ነው: እኛም ብሃገቨድ ጊታን ሳንቀይር እንደ አለ:እያቀረብን ነው: