AM/Prabhupada 0175 - ድሀርማ ማለት ቀስ በቀስ ቁራዎችን ወደ ዝይ ወይንም ስዋን መቀየር ማለት ነው፡፡

The printable version is no longer supported and may have rendering errors. Please update your browser bookmarks and please use the default browser print function instead.


Lecture on SB 1.8.33 -- Los Angeles, April 25, 1972

ማንኛውም ስነጽሁፍ:ከአምላክ ጋር ያልተገናኘ ከሆነ:“ታድ ታድ ቫያስያም ቲርትሃም” ይህም የሚታየው ልክ እንደ ቁራዎች እንደሚደሰቱበት ቦታ ነው: ቁራዎች የሚደሰቱበት ቦታ የት ነው? ይህም በቁሻሻ ቦታ ነው: ነጭ ስዋኖች ደግሞ የሚደሰቱበት በጠራ ውሃ:አትክልትና እና ወፎች ባሉበት አካባቢ ነው: እንደዚሁም ሁሉ በእንስሳዎች ደረጃ እንኳን ልዩነት አለ: የስዋን ደረጃ እና የቁራ ደረጃ:የተፈጥሮ ክፍልፍል አለው: ስዋን ወደ ቁራ አይሄድም:ቁራም ደግሞ ወደ ስዋን ቦታ አትሄድም: በሰው ፍጥረትም ደግሞ እንደ ስዋን ደረጃ ያሉ እና እንደ ቁራ ደረጃ ያሉ ሰዎች አሉ: የስዋን ደራጃ ያሉ ወደ እዚህ ይመጣሉ:ምክንያቱም ሁሉም ነገር ንጽህና ያለው ነው: ጥሩ:ፍልስፍና:ምግብ:ትምህርት:ልብስ:አስተሳሰብ: ሁሉም ጥሩ ሁኖ ይገኛል: የቁራ ደረጃ ሰዎች:ክለብ:ፓርቲ:የራቁት ዳንስ የመሳሰሉት ቦታዎች ለመሄድ ይመርጣሉ: ይህ የክርሽና ንቃተ ማህበር ግን የተቋቋመው እንደ ስዋን ደረጃ ላሉ ሰዎች ነው: ለቁራ ደረጃ ለሆኑ ሰዎች አይሆንም: ነገር ግን:እንደ ቁራ የሆኑትን ሰዎች:ወደ ስዋንነት መቀየር እንችላለን:ይህ ነው የእኛ ፍልስፍና: ቁራ የነበረው እንደ ስዋን እንዲዋኝ እናደርገዋለን: ይህ ነው የክርሽና ንቃት: ስዋኖች እንደ ቁራ ሲሆኑ:ይህም የአለማዊ ኑሮ ነው: ክርሽናም እንዲህ ብሏል:“ያዳ ያዳ ሂ ዳሃርማስያ ግላኒር ብሃቫቲ (ብጊ4 7) ህያው ነፍስ በዚህ ገላ ውስት ተጠምዶ:ስሜቱን ለማርካት ይጥራል: በየአዲስ ህይወቱም የገላ ገላ እየቀያየረ ይገኛል:ይህ ነው ሁኔታው: ድሃርማ ማለት ደግሞ ቁራዎችን ወደ ስዋን መመለስ ማለት ነው:ይህ ድሃርማ ነው: ልክ አንድ ሰው:ያልተማረ:ባህል የሌለው:ሊሆን ይችላል:ነገር ግን ወደ ተማረ እና ባህላዊ ሰው ለመቀየር ይችላል: ይህም በትምህርት እና:በልምምድ ነው:ስለዚህ ይህም እድል ለሰው ህይወት አለ: ውሻን ድቮቲ ለማድረግ ማስተማር አልችልም: ሊደረግም ይቻላል:ግን እኔ ለዚህ ሃይል የለኝም:ይህም በቼይታንያ ማሃብራብሁ ተደርጓል: አንድ ግዜም ጃሪካንድ በሚባል ጯካ ያልፍ ነበር:እዚህም ነብሮቹን:እባቦቹን:አጋዘኖቹን:እና የተለያዩትን እንስሶች:ደቮቲ አደረጋቸው: እንደዚህም ይህ በቼይታንያ ማሃብራብሁ ተችሎ ነበረ:ምክንያቱም እርሱ አምላክ ነው:የፈለገውንም ማድረግ ይችላል:እኛ ይህን ማድረግ አንችልም: ቢሆንም ግን እኛ በሰው ልጅ ህብረተሰብ ውስጥ መስራት እንችላለን:ምንም እንኳን የሰው ልጅ የወደቀ ቢሆንም: የእኛን ትእዛዝ ከተከተለ:መቀየር ይችላል: ይህ ድሃርማ ይባላል:ድሃርማ ማለት አንድን ወደ ነበረበት መንፈሳዊ ደረጃ መመለስ ማለት ነው: ያም ድሃርማ ነው:የተለያየ ዲግሪ ሊኖረው ይችላል: የነበርንበት ደረጃ እኛ የአምላክ መንፈዋዊ ወገን እና ፍንጥቃዊ ነን: ይህንንም ስንረዳ:እኛ የአማላክ ወገን እና ፍንጥቃዊ:ያ የእኛ ትክክለኛ ስፍራችን ነው: ይህም ብራህማ ብሁታ ይባላል:(ሽብ4 30 20) የብራህማን ደራጃችንን ለይተን ማወቅ እና መገንዘብ ማለት ነው: