AM/Prabhupada 0205 - እነዚህ ሰዎች ይህንን ያህል የክርሽና ንቃትን ይቀበሉታል ብዬ አልገመትኩም ነበረ፡፡

The printable version is no longer supported and may have rendering errors. Please update your browser bookmarks and please use the default browser print function instead.


Morning Walk -- May 20, 1975, Melbourne

ፕራብሁፓድ:ስትሰብኩ:የግድ የክርሽና ንቃት መውሰዱን ማየት የለባችሁም:ክርሽና ንቃትን ማዳበር ቀላል ነገር አይደለም: ቀላል አይደለም:ብዙ ትውልድም ሊጠይቅ ይችላል:“ባሁናም ጃንማናም አንቴ” (ብጊ 7 19) ነገር ግን ሃላፊነታችሁን መወጣት አለባችሁ:“ያሬ ዴክሃ ታሬ ካሃ ክርሽና ኡፓዴሽ” (ቼቻ ማድህያ 7 128) ስትሰብኩ ሃላፊነታችሁን ተወጣችሁ ማለት ነው: በእርግጥ እንዲቀበሏችሁ ለማድረግ ጥረት ያስፈልጋል: ሊቀበሏችሁ ካልቻሉ ግን:ያ የእናንተ የስራ መዘናጋት እና መሳሳት አይደለም: ሃላፊነታችሁ ሂዶ መስበክ ብቻ ነው: ልክ እኔ ወደ አገራችሁ ስመጣ:ምንም ነገር ይሳካል ብዬ አልጠበቅሁም ነበር: ምክንያቱም:ልክ እንደዚህ ስል:”ማመንዘር:ስጋ መብላት:አይፈቀድም“ ስል ትተውኝ ይሄዳሉ ብዬ ነበር:(ሳቅ) ስለዚህ ተስፋም አልነበረኝም: ድቮቲ 1:እነዚህን በጣም ይወዳሉ:

ፕራብሁፓድ:አዎን:ነገር ግን በእናንተ ሩሁርሁነት ተቀብላችሁኛል:ነገር ግን የጠበቁት ነገር አልነበረም: እነዚህ ሰዎች ይቀበሉኛል ብዬ በፍጹም አልጠበኩትም: ሀሪ ሶሪ:በክርሽና መተማመን አለብን:

ፕራብሁፓድ:አዎን:ያ ነው የእኛ ሃላፊነት: ሀሪ ሶሪ:ውጤቱን ከጠበቅን:

ፕራብሁፓድ:የመንፈሳዊ አባታችንን እንደ አዘዘን: ሃላፊነታችንን መወጣት አለብን: ”ጉሩ ክርሽና ክርፓያ“ (ቼቻ ማድህያ 19 151) እንደዚሁም ሁሉ ከሁለቱም ወገን ትካሳላችሁ:ከመንፈሳዊ አባት እና ከክርሽና: ይህም የህይወታችሁ መሳካት ነው: