AM/Prabhupada 0220 - እያንዳንዱ ነዋሪ ነፍሳት የአብዩ ጌታ ቅንጣፊ አካል እና ወገን ነው፡፡

Revision as of 13:00, 8 June 2018 by Vanibot (talk | contribs) (Vanibot #0019: LinkReviser - Revised links and redirected them to the de facto address when redirect exists)
(diff) ← Older revision | Latest revision (diff) | Newer revision → (diff)


Arrival Lecture -- Paris, July 20, 1972

በመንፈሳዊ ደረጃ ላይ የሚገኝ ምሁር ሰው የተማረ ብራህማና እና ውሻ መንገድ ላይ ቢያይ ሁለቱም በቀድሞ የፍጥራታቸው ካርማ የተለያየ ገላ ለመያዝ እንደበቁ ይረዳል። ነገር ግን በውስጣቸው የተመሰላለ ነፍስ እንዳላቸው የተረዳ ነው፡፡ ሰለዚህ በቁሳዊ ወይንም ዓለማዊ አስተሳሰብ ለያይተን እናስባለን፡፡ “እኔ ህንድ ነኝ፡፡ እኔ ፈረንሳዊ ነኝ፡፡” ”እርሱ እንግሊዛዊ ነው፡፡ እርሱ አሜሪካዊ ነው፡፡ እርሱ ድመት ነው፡፡ እርሱ ውሻ ነው፡፡“ ይህ በቁሳዊ ዓለም የተመሰረተ የዓለማዊ አስተያየት ነው፡፡ በመንፈሳዊ ደረጃ ግን ሁሉም ፍጥረት ነፍስ ወይንም የአብዩ አምላክ ወገን እና ቁራሽ እንደሆነ ለመረዳት እንችላለን፡፡ ይህም በብሀገቨድ ጊታ ውስጥ ተጠቅሷል፡፡ “ማም ኤቫምሳ ጂቫ ብሁታ” እያንዳንዱ ፍጡር ምንም ዓይነት ነፍስ ያለው ፍጥረት ሁሉ በዚህ ይዕይንተ ዓለም ውስጥ 8,400,000 የሚሆኑ የተለያዩ ፍጥረታት አሉ፡፡ ነፍስ ቢሆኑም ግን እያንዳንዳቸው የተሸፈኑት በተለያየ ገላ ነው፡፡ ልክ በዚህ ዓለም እንደምናየው ፈረንሳዊ ሰው የተለየ ልብስ ሊለብስ ይችላል፡፡ እንግሊዛዊውም የተለየ ልብስ ይለብሳል፡፡ ሕንዱም የተለየ ልብስ ይለብሳል፡፡ ዋናው አስፈላጊው ግን ልብሱ አይደለም፡፡ አስፈላጊው ልብሱን የለበሰው ሰው ነው፡፡ እንደዚሁም ሁሉ ይህ የለበስነው ገላ እንደ ነፍስ አስፈላጊ አይደለም፡፡ “አንታቫንታ ኢሜ ዴሀ ኒትያስዮክታሀ ሻሪሪናሀ“ (ብጊ፡ 2 18) ይህ ገላ ጠፊ ነው፡፡ ነገር ግን በገላው ውስጥ የሚገኘው ነፍስ ለዘለዓለም ጠፊ አይደለም፡፡ ሰለዚህ ይህ የሰው ልጅ ሕይወት ዓላማ ይህንን ሊጠፋ የማይችለውን የነፍስ እውቀት ለማዳበር ነው፡፡ የሚያሳዝነው ነገር ቢኖር የእኛ የሳይንስ እውቀት ወይንም ትምህርት ቤት ኮ ሌጅ ዩኒቨርስቲ የምንማረው እውቀት ሁሉም የሚያሰተምሩን ሰለ ጠፊ ሰለሆነው የቁሳዊው ዓለም ብቻ ነው፡፡ ጠፊ ሰላልሆነው የነፍስ እውቀት አይደለም፡፡ የዚህም የክርሽና ንቃተ ማህበር ዓላማ ይህንንም የማይጠፋውን የነፍስ እውቀት ለማስተላለፍ ነው፡፡ ይህም የነፍስ እውቀት እንቅስቃሴ ነው፡፡ ይህ የፖሎቲካ እንቅስቃሴ አይደለም ወይንም የህብረተሰብ ማህበር ወይንም ሌላ የሀይማኖት ማህበር አይደለም፡፡ እነርሱ ሀሳባቸው ሁሉ ሰለ ወዳቂው ገላ ምቾት ነው፡፡ የክርሽና ንቃት የሚያሰተምረው ግን ሰለ ዘለዓለማዊው ነፍስ ነው፡፡ ሰለዚህም በሳንኪርታን እንቅስቃሴያችን እንደሚካሄደው ሁሉ የሀሬ ክርሽናን ቅዱስ ስሞች በመዘመር ልብችን ቀስ በቀስ ሊፀዳ ይችላል፡፡ በዚህም ሂደት ወደ መንፈሳዊ ደረጃ ለመድረስ እንችላለን፡፡ ለምሳሌ እንደምታዩት በዚህ እንቅስቃሴያችን ውስጥ ከተለያዩ አገራት እና ከተለያዩ የሀይማኖት ድርጅቶች የመጡ ተማሪዎች እናያለን፡፡ ነገር ግን ማናቸውም ቢሆኑ የመጡበትን ሀይማኖት ዜግነት ወይንም ጎሳ እና የቀለም ልዩነት አያዩም፡፡ እያንዳንዳቸው እራሳቸውን የሚያዩት ልክ የሽሪ ክርሽና ወገን እና ቁራሽ እንደሆኑ ብቻ ነው፡፡ በዚህም ዓይነት ንቃት እና እራሳችንንም በዚህ ንቃት ተግባራዊ ሕይወት ውስጥ ካሰማራን ፍፁም ነፃነትን አገኘን ማለት ነው፡፡ ሰለዚህ ይህ የክርሽና ንቃት እንቅስቃሴያችን በጣም አስፈላጊ ነው፡፡ መቸም ሁሉን የሚያሰፈልገውን መረጃ ሁሉ በትንሽ ደቂቃ ውስጥ ለመስጠት አይቻልም፡፡ በዚህም ንቃት ፍላጎት ያደረባችሁ ሁሉ እኛን መድረስ እና ማነጋገር ትችላላችሁ፡፡ ይህም በመላላክም ሆነ መፃህፍቶቻችንን በማንበብ ወይንም በግል በመገናኘት ሊሆን ይችላል፡፡ በዚህም ሂደት ሕይወታችሁ የተሳካ ይሆናል፡፡ እኛ በመለያየት ከፋፍለን አናይም፡፡ ”ይህ ህንድ ነው፡፡ ይህ እንግሊዝ ነው፡፡ ይህ ፈረንሳዊ ነው፡፡ ይህ አፍሪካዊ ነው፡፡“ ነገር ግን እኛ ሁሉን የምናየው የአብዩ አማላክ ቅንጣፊ መንፈሳዊ አካል እንደመሆኑ ነው፡፡ ይህም ለሰው ልጅ ብቻ ሳይሆን እንስሳዎችንም ጭምር ነው፡፡ ወፎችን አውሬዎችን ዛፎችን የባህር ፍጥረታትን ትላትሎችም ሁሉ የአብዩ ፈጣሪ አምላክ ወገኖች የሆኑ ዘለዓለማዊ ነፍሳት ናቸው፡፡