AM/Prabhupada 0321 - እራሳችሁን ሁል ግዜ እንዴት ከዓብዩ ጌታ የሀይል ማመንጫ ጋር ለመገናኘት እንደምትችሉ ጥረት አድርጉ፡፡

The printable version is no longer supported and may have rendering errors. Please update your browser bookmarks and please use the default browser print function instead.


Lecture on SB 1.15.28 -- Los Angeles, December 6, 1973

ቼይታንያ ማሃፕራብሁ እንደ ሃላፊነታችሁ ስራ መፈጸም ይገባችኋል ብሏል: እንደታዘዘው:”አፓኒ አቻሪ“ ከዚያም ሌላውን ማስተማር ይገባችኋል: እራሳችሁም በተግባር ካላሳያችሁ:ቃላቶቻችሁ ምንም ዋጋ አይኖራቸውም: ”ኤቫም ፓራምፓራም ፕራምታም“ (ብጊ 4.2) ከዋናው የኤሌክትሪክ ማከፋፈያ ድርጅት ጋር የተያያዛችሁ ከሆነ:ኤሌክርትሪክ ማግኘት ትችላላችሁ አለበለዛ ግን የኤሌክትሪክ ገመድ ማንጠልጠል ምን ዋጋ ይኖረዋል? ገመዱ ብቻ ምንም ሊጠቅማችሁ አይችልም:ከማከፋፈያው ጋር መያያዝ ያስፈልጋችኋል: የተያያዘው ከተቆረጠም የገመዱ መንጠልጠል ዋጋ አይኖረውም: ስለዚህም የክርሽና ንቃት እንቅስቃሴ ማለትም:እራሳችንን ከዋናው የማከፋፈያው ድርጅት ማገናኘት ማለት ነው: እንደዚሁም ሁሉ በየሄዳችሁበት:ብርሃን ይኖራል: ከልተገጣጠማችሁ ደግሞ:ብርሃን ሊኖር አይችልም: አምፖሉ አለ:ኮረንቲ ክሩም አለ:ማብሪያ ማጥፊያውም አለ:ሁሉም ነገር አለ: አርጁናም እንዲህ ነው የተሰማው:”እኔ ያው እራሱ አርጁና ነኝ“ ”በኩሩክ ሼትራ የተዋጋሁ እኔ ራሱ አርጁና ነኝ“ ”በጣም ታላቅ ተዋጊ ተብዬ የምጠራ ሰው ነበርኩኝ:ይህም እራሱ የእኔ ደጋን ነው:ቀስቶቼም እራሳቸው የእኔ ቀስቶች ናቸው“ ”አሁን ግን ዋጋ ቢስ እንደሆንኩ ይሰማኛል:ክርሽናም አጠገቤ ስለሌለ:እራሴን ለመከላከል አልቻልኩም“ “ክርሽናም አጠገቤ የለም” እንዲህም እያለ:ክርሽና የነገረውን ሁሉ ማስታወስ ጀመረ: ይህም በኩሩክሼትራ ጦርነት ላይ እያለ: የተማረውን ነው: ክርሽና ከቃሉ በምንም አይለይም:ይህ ፍጹም እውነት ነው: ክርሽና 5000 አመት በፊት የተናገረውን:አሁን መከተል ብትጀምሩ:ወዲያውኑ ከክርሽና ጋር መግናኘት ትችላላችሁ: ይህ ነው ስርአቱ:አርጁናንም እዩት:እንዲህም አለ:”ኤቫም ቺንታያቶ ጂሽኖ ክርሽና ፓዳ ሳሮሩሃም“ ክርሽናን ሲያስታውስ እና:በጦር ሜዳም ላይ የተቀበለውንም መመሪያ ሲያስታውስ: ወዲያውኑ አንደበቱ በሰላም ”ሻንታ“ ተሞላ:ከጭንቀቱም ወረደ:ይህ ነው ስርአቱ: ከክርሽና ጋር የጠበቀ ግንኙነት አለን:ይህም ዘለአለማዊ ነው:ይህም ሰውሰራሽ አይደለም: እንደዚሁም እራሳችንን ከክርሽና ጋር ሁልግዜ የምናያይዝ ከሆነ:በህይወታችን ምንም ረብሻ አይኖርም: ”ሰላምተኛ“ “ያም ላብድህቫ ቻፓራም ላብሃም ማንያቴ ናድሂካም ታታሃ” ይህንንም የሰላም መድረክ ካገኛችሁ:የንቃቱ ትቁ ትርፍ:ወይንም ትልቁ ገቢ ነው: “ያም ላብድቫ ቻ" ከዚህም የተለየ:ሌላ ምኞትም ሊኖራችሁ አይችልም: ከፍትኛም ገቢ ወይንም ትርፍ እንዳላችሁ ሁኖ ይሰማችኋል: ”ያም ላብድህቫ ቻፓራም ላብሃም ማንያቴ ናድሂካም ታታሃ ያስሚን ስትሂታሃ“ በዚህም ደረጃ ላይ ሁናችሁም ከረጋችሁ:”ጉሩናፒ ዱህኬና“ (ብጊ 6.20-23) በጣም ከባድ የሚባለው እንኳን አደጋ:ሊረብሻችሁ አይችልም: ይህም ሰላም ነው:ትንሽ በቆረቆረን ግዜም የምንረበሽ ከሆነ ግን:ይህ ሰላም አይደለም: በክርሽና ንቃትም የረጋችሁ ከሆነ:በትልቅም አደጋ ቢሆን ልትረበሹ አትችሉም: ይህ ነው የክርሽና ንቃት ብቁነት: አመሰግናለሁ: