AM/Prabhupada 0340 - እኛ በተፈጥሮ መሞት የሚገባን አይደለንም፡፡ ነገር ግን በተፈጥሮ ሞትን ለማየት ተገደናል፡፡

Revision as of 13:04, 8 June 2018 by Vanibot (talk | contribs) (Vanibot #0019: LinkReviser - Revised links and redirected them to the de facto address when redirect exists)
(diff) ← Older revision | Latest revision (diff) | Newer revision → (diff)


Lecture on BG 9.1 -- Melbourne, June 29, 1974

“ናሞ ማሃ ቫዳንያያ ክርሽና ፕሬማ ፕራዳያቴ:ክርሽናያ ክርሽና ቼይታንያ:ናምኔ ጎውራ ትቪሼ ናማሃ” (ቼቻ ማድህያ 19.53) ሽሪላ ሩፓ ጎስዋሚ:ሽሪ ቼይታናያ ማሃ ፕራብሁን ፕራያግ ውስጥ ሲያገኛቸው: በህንድ አገር ውስጥ ፕራያግ የሚባል ቦታ አለ: ሽሪ ቼይታንያ ማሃ ፕራብሁም:የሳንያሳ የመነኩሴ ስርአቱንም እንደ ጨረሰ: ወደ ፕራያግ እና ወደ ሌላ ቅዱስ ቦታዎች ሂዶ ነበር: ሽሪላ ሩፓ ጎስዋሚም የመንግስት ሚኒስቴር ነበረ: ሁሉን ግን እርግፍ አድርጎ ለመንፈሳዊ አለም ብሎ ተወ:የሀሬ ክርሽናንም እንቅስቃሴ ከሽሪ ቼይታንያ ጋር ገጠመ: መጀመሪያ ላይም እንደተገናኙ:ይህንን ጥቅስ አቀረበ:“ናሞ ማሃ ቫዳንያያ” “ቫዳንያያ” ማለት “በጣም የገነነ ነው ማለት ነው” የተለያዩ የአምላክ ወገኖች በአለም ላይ ይመጣሉ:ነገር ግን ሩፓ ጎስዋሚ እንዲህ አለ: ይህ የአምላክ ወገን ቼይታንያ ማሃ ፕራብሁ በጣም የገነነ ነው: “ናሞ ማሃ ቫዳንያያ” ለምንድነው በጣም የገነነው? ክርሽና ፕሬማ ፕራዳያቴ:“ክርሽናን በዚህ በክርሽና ንቃት እንቅስቃሴህ እየሰጠህ ነው” ክርሽናን መረዳት በጣም አስቸጋሪ ነው: ክርሽናም በብሃገቨድ ጊታ እንዲህ ብሏል:“ማኑሽያናም ሳሃሽሬሹ ካሽቺት ያያቲ ሲድሃዬ (ብጊ 7.3) ”ከብዙ ሚሊዮን ሰዎች መሃከል:በዚህ ዘመን ብቻ ሳይሆን:ከዚህ ዘመንም በፊት“ ማኑሽያናም ሳሃሽሬሹ:”ከብዙ ሚሊዮን ህዝብ መሃከል “ካሽቺት ያያቲ ሲድሃዬ” አንድ ሰው ብቻ ከልቡ ነጹህ እና ፍጹም መሆን ይፈልጋል: በጠቅላላው አነጋገር:ፍጹም መሆን ምን እንደሆነም አያውቁትም:ህይወት ማሳካት ምን እንደሆነ አያውቁትም: ይህም ማለት መወለድን:መሞትን:ማረጅን:መታመምን ማቆም ማለት ነው:ይህ ነው ህይወትን ማሳካት ማለት: ሁሉም ለማሳካት ይሞክራል:ነገርግን ይህ ምን እንደሆነ አልተረዱም: ህይወት ማሳካት ማለት:ከእነዚህ አራት ነፃ መሆን ማለት ነው: ምንድን ናቸው? መወለድ:መሞት:ማረጅ: መታመም:ሁሉም ማንም መሞት አይፈልግም:ግን ይህ ግዳጅ ነው:መሞት አለብን: ይህ ያልተሳካ ሁኔታ ነው:እነዚህ ተንኮለኞች:ይህን አይረዱም:መሞት ያለ ነው ይላሉ:ይህ ልክ አይደለም: ምክንያቱም ነፍስ ዘላለማዊ ናት:መሞትም የለብንም:ግን ተፈጥሮ ይህንን ፈጥሯል: ይህም መቆም አለበት: