AM/Prabhupada 0405 - የሰይጣን አንደበት ያላቸው አብዩ ጌታ አብይ ሰው እንደመሆኑ ለመረዳት ያዳግታቸዋል፡፡ ይህም የከሀዲያን አስተሳሰብ ነው፡፡

The printable version is no longer supported and may have rendering errors. Please update your browser bookmarks and please use the default browser print function instead.


Lecture on SB 7.7.30-31 -- Mombassa, September 12, 1971

ሰይጣናዊ አንደበት ያላቸው አምላክ ሰው መሆኑን አይረዱም:ይህም ሰይጣናዊ ነው: ሊረዱት አይችልም:ይህም ከእራሳቸው ጋር አምላክን ሊያወዳድሩ ስለሚፈልጉ ነው: ዶክተር እንቁራሪት:እንደዚህ ነው ታሪኩ አትላንቲክ ውቅያኖስን ለመረዳት ፈለገ ይህንንም ያመዛዝን የነበረው 3 ፊት ከምትሆነው ኩሬው ነው: ስለ አይቶት የማያውቀውን አትላንቲክም ሲያጫውቱት:እርሱም ከራሱ ትንች ኩሬ ጋር ማወዳደር ጀመረ: 4 ወይንም 5 ፊት ሊሆን ይችላል:ወይንም 10 ፊት ብሎ ያሰባል:ይህም ከራሱ 3 ፊት ጋር ስለሚያወዳድረው ነው: ይህም ጓደኛው ትልቅ ውቅያኖስ አይቼ መጣሁ ስለአለው ነው: ይህንንም ግዙፍነት ባለው ልምድ ለማመሳከር ፈለገ: የኔ ይህን ያህል ነው እያለም ማሰላሰል ቀጠለ:3 ፊት 4 ፊት 5 ፊት ነገር ግን በሚሊዮን ፊትም ማሰላሰል ቢሞክር ትልቅነቱን ሊረዳ አይችልም: እንደዚህም እነዚህ ከሃዲያን እና ሰይጣናውያን:አምላክን እንደራሳቸው እየቆጠሩ ማወዳደር ይፈልጋሉ: ክርሽና እንዲህ ሊሆን ይችላል:ክርሽና እንዲህ ሊሆን ይችላል: በጠቅላላው አነጋገር እነርሱ እና ክርሽና አንድ እንደሆኑ አድርገው ያስባሉ:እንዴትስ ይህ ሊሆን ይችላል? ክርሽና አብይ እንደሆነ አያምኑም: አምላክ እንደ እኔ ነው ብለው ያስባሉ:እኔም አምላክ ነኝ:ይህ ሰይጣናዊ አስተሳሰብ ነው: