AM/Prabhupada 0444 - ጐፒዎች በቁሳዊ ዓለም ውስጥ ውስን የሆኑ ነፍሳት ሳይሆኑ በንፁህ መንፈሳዊነታቸው ነፃ የሆኑ ናቸው፡፡

The printable version is no longer supported and may have rendering errors. Please update your browser bookmarks and please use the default browser print function instead.


Lecture on BG 2.8-12 -- Los Angeles, November 27, 1968

ፕራሁፓድ:ህምምም?

ድቮቲ:አንድ ቦታ የፃፍከውን አንብቤ ነበረ: ስለ ራድሃ ክርሽና ሚስትራዊ እውቀትን ስለማወቅ: አንድ ሰው ጎፒዎችን ማገልገል አለበት:ጎፒዎችም የጎፒዎች አገልጋዮች ናቸው: እና አንተም የጎፒዎች አገልጋይ ነህ ብዬ አስብኩ: ይህ ትክክል ነውን? ወይንም እንዴት አድርገን ነው የጎፒዎቹን አገልጋዮች ለማገልገል የምንችለው?

ፕራብሁፓድ:ጎፒዎች በዚህ አለም እንደኛ የተወሰኑ ነፍሶች አይደሉም: እነርሱ ነፃ የወጡ ነፍሶች ናቸው: በመጀመሪያ ደረጃ:አንተ ከዚህ ከአለማዊ ውስን ኑሮ መውጣት አለብህ: ከዛም ጎፒዎቹን የማገልገል ጥያቄ ይመጣል: በአሁኑ ግዜህ ጎፒዎችን በቀጥታ ለማገልገል አትሻ: ከዚህ አለማዊ ውስን ኑሮ ግን ለመውጣት ሞክር: ከዚያም ጎፒዎቹን ለማገልገል የምትችልበት ግዜ ይመጣል: በዚህ በአለማዊ የወተሰነ ኑሮአችን:ማገልገል አንችልም:ክርሽና እያደረገው ነው: ነገር ግን:ክርሽና በ”አርቻ ማርጋ“ አማካኝነት እድሉን ሰጥቶናል: ልክ ለክርሽና ደይቲ ፕራሳድ እንደምናቀርብለት:መመሪያችንን እየተከተልን: እንዲህም መግፋት አለብን:መዘመር እና መስማት: ቤተ መቅደስም መስገድ:አራቲ እና ፕራሳድም ማቅረብ: እንዲህ እያደረግንም ስንራመድ:ክርሽና ሁሉን ሊከፍትልን ይችላል: የራሳችሁንም ሁኔታ ምን ላይ እንዳለ ትረዱታላችሁ: ጎፒዎች ማለት ሁልግዜ አምላክን በማገልገል ላይ የሚገኙ ማለት ነው: ይህም የዘላለማዊ ግኑኝነት ወደፊት ይገለጻል:መጠብቅም አለብን: ወዲያውኑ ግን እንደጎፒዎቹ ለመምሰል አይገባንም ጎፒዎችን ለማገልገል ጥሩ ሃሳብ ነው:ነገር ግን ይህ ብዙ ግዜ ይፈልጋል:ወዲያውኑ አይሆንም: አሁን ወዲያውኑ ማድረግ ያለብን ግን:ህግጋት እና መመሪያችንን መከተል እና ሃላፊነታችንን መወጣት ብቻ ነው: