AM/Prabhupada 1067 - ብሀገቨድ ጊታን መቀበል ያለብን ምንም የግል ትርጉም ሳንጨምር ወይንም መልእክቱን ሳናጓድል መሆን አለበት፡፡

Revision as of 13:10, 8 June 2018 by Vanibot (talk | contribs) (Vanibot #0019: LinkReviser - Revised links and redirected them to the de facto address when redirect exists)
(diff) ← Older revision | Latest revision (diff) | Newer revision → (diff)


660219-20 - Lecture BG Introduction - New York

ጉድለት ያማይሳነውን አብዩ ጌታን ለመረዳት በዚህ ምድር ላይ ሕያው ነፍሳት የተሟላ እና የተደራጀ እድል አላቸው፡፡ በዚህ ምድር ላይ ጉድለት ያለባቸው ነገሮች እንዳሉ የሚሰማንም ጉድለት ስለማይሳነው አብዩ ጌታ ሙሉ እውቀት ስለሌለን ነው፡፡ ብሀገቨድ ጊታ ስለ ቬዲክ ብልሀቶች የተሟላውን እውቀት ይዞልን አቅርቦልናል፡፡ መላው የቬዲክ እውቀት ለዘለዓለምም ቢሆን ፍፁም ወዳቂ አይደለም፡፡ ይህም የቬዲክ እውቀት እንዴት ፍፁም ወዳቂ እንዳልሆነ በተለያየ መንገድ ለመረዳት እንችላለን፡፡ ለምሳሌ ሂንዱዎችን ብንወስዳቸው እንዴት የቬዲክ እውቀትን በሙሉ ልቦናቸው እንደሚቀበሉት ከሚከተለው ቀላል ምሳሌ ለመረዳት እንችላለን፡፡ ለምሳሌ የላም እበትን እንውሰድ፡፡ የላም እበት ማለት የእንስሳ ሰገራ ማለት ነው፡፡ ነገር ግን "ስምርቲ" ተብሎ በሚታወቀው የቬዲክ ብልሀት እና እውቀት ውስጥ እንደተገለፀው አንድ ሰው የእንስሳን ሰገራ ከነካ ገላውን በመታጠብ እራሱን ማጽዳት ይገባዋል ተብሎ ተጠቅሷል። ቢሆንም ግን በቬዲክ ስነጽሁፎች ውስጥ የላም እበት ንፁህ እንደሆነ ተደርጎ ተገልጿል፡፡ እንዲያውም የተበከሉ እና ንፁህ ያልሆኑ ቦታዎችን ሁሉ በላም እበት በመለቅለቅ እንዲፀዱ ተመክሯል፡፡ ይህንንም በመገንዘብ አንድ ሰው እንዴት በአንድ ወገን ቬዳዎች የእንስሳን ሰገራ ንፁህ እንዳልሆነ ሲገልፁ በሌላ ወገን ደግሞ እንዴት የላም እበት የእንስሳ ሰገራ ሆኖ እያለ ንፁህ ነው ተብሎ በተቃራኒነቱን ለመቀበል እንችላለን ብለው ሊከራከሩ ይችላሉ፡፡ ይህም የተቃረነ አነጋገር ሊመስል ይችላል፡፡ ቢሆንም ግን ይህ የቬዲክ እውቀት መመርያ ስለሆነ ተቀብለነው በተግባር እንገልፀዋለን፡፡ ይህንንም የተቃረነ የሚመስል መልእክት በተግባር በመቀበላችን ስህተት ላይ ልንወድቅ አንችልም፡፡ ይህም በግዜው በሚገኘው የኬሚስትሪ ምርምር እና በሳይንስ የተደገፈ ነው፡፡ አንድ “ላል ሞሀን ጎሳል” የተባለ ዶክተርም የላም ኩበትን በጥልቅ ምርምር አድርጎ የላም ኩበት የተለያዩ ጀርሞች እንዳይበክሉ ለመከላከል የሚችል ባህርይ እንዳለው በምርምር አግኝቶታል፡፡ እንደዚሁም ሁሉ የጋንጀስ ወንዝ ውሀንም ለምርምር ወስዶ ጥናት አድርጎ ነበረ፡፡ ስለዚህ የምሰጠው መልእክት ቢኖር የቬዲክ እውቀት የተሟላ እና ከሁሉም ዓይነት ጥርጣሬ እና ስህተቶች ነፃ የሆነ ነው፡፡ ስለዚህ ብሀገቨድ ጊታ ከቬዲክ እውቀቶች ሁሉ የነጠረው እውቀት ነው፡፡ የቬዲክ እውቀት ሊወድቅ የማይችል ነው፡፡ የወረደውም የድቁና ስርዓትን ይዞ ለዘመናት ሲወርድ ሲዋረድ ነው፡፡ የቬዲክ እውቀት በሰው ልጅ ምርምር የተዘጋጀ እወቀት አይደለም፡፡ የእኛ ምርምር ሁሉ የተሟላ ሆኖ ሊገኝ አይችልም፡፡ ምክንያቱም የምናደርገው ምርምር ሁሉ የተሟላ ሀይል በሌላቸው ስሜቶቻችን ነው፡፡ ስለዚህ የምርምራችን ውጤት ሁሉ ያልተሟላ ሆኖ ይገኛል፡፡ የተሟላ እውቀት ለማግኘት አዳጋች ሆኖ እናገኘዋለን፡፡ ስለዚህ መቀበል ያለብን የተሟላውን እውቀት ብቻ ነው፡፡ ይህም የተሟላው እውቀት በብሀገቨድ ጊታ ውስጥ ተገልጾልን ይገኛል፡፡ እንደጀመርነውም "ኢቫም ፓራም ፓራ ፕራፕታም ኢማም ራጃርሳዮ ቪዱህ" (ብጊ 4.2) መውስድ የሚገባን እውቀት ከትክክለኛው ምንጭ መሆን አለበት፡፡ ይህም ከዓብዩ ጌታ ጀምሮ በድቁና ስርዓት ሲወርድ ሲዋረድ ከመጣው የመንፈሳዊው የድቁና ስርዓት ነው፡፡ ብሀገቨድ ጊታ የተዘመረው በዓብዩ ጌታ እንዲሁም በአርጁና ነው፡፡ አርጁና የብሀገቨድ ጊታን ትምህርት ከክርሽና የወሰደው ነው፡፡ አርጁናም ይህንን እውቀት ምንም ነገር ሳያጓድል በሙሉ መንፈስ ተቀብሎታል፡፡ መልእክቱን እንደአሻን መርጦ መውሰድም አግባብ አይደለም፡፡ የተወሰነውን የብሀገቨድ ጊታ መልእክት ወስደን ሌላውን መግደፍ አንችልም፡፡ ይህ ተቀባይነት የለውም፡፡ ብሀገቨድ ጊታን መቀበል ያለብን ምንም የግል ትርጉም ሳንሰጠው እና ምንም ሳናጎድል መሆን አለበት፡፡ እንዲሁም የግላችንን ፍላጎት ሳንጨምርበት መሆን አለበት፡፡ መወሰድ ያለበትም ፍፁም እንደተሟላ የቬዲክ እውቀት ነው፡፡ ይህ የቬዲክ እውቀት የቀረበው ከመንፈሳዊ ምንጭ ነው፡፡ ምክንያቱም የመጀመሪያው ቃል የቀረበው ወይንም የተነገረው በዓብዩ የመላእክት ጌታ ነው፡፡ እነዚህም በአብዩ ጌታ የተነገሩት ቃላቶች "አፖሩሴያ" ተብለው ይታዋቃሉ፡፡ ስለዚህ የቬዲክ ትምህርቶች የቀረቡት በምድር ከሚገኙ ተራ ሰዎች አይደለም፡፡ በምድር የሚገኘው የሰው ዘር በአራት ዓይነት የስህተት ዘርፎች የሚጠቃ ነው፡፡ በዚህ ምድር ላይ የሚገኙ ፍጥረታት ሁሉ በአራት ዓይነት ስህተቶች ሲጠቁ ይታያሉ፡፡ እነዚህም 1) በስራቸው ሁሉ ለስህተት የተጋለጡ ናቸው፡፡ 2) በምትሀት ውስጥ በመግባት ግር ብሏቸው ይገኛሉ፡፡ 3) በማታለል ባህርይ ሲጠቁ ይታያሉ፡፡ 4) ፍፁም የተሟላ ሀይል ከሌላቸው ለስህተት ከሚያጋልጡን ስሜቶቻችን ጋር እንኖራለን፡፡ በእነዚህም አራት ዓይነት ድክመቶች ተጠቅተን በመገኘት ፍፁም የሆነውን እውቀት እና ጥልቀት ያለውን እውቀት ልናቀርብ አንችልም፡፡ የቬዳ እውቀቶች እንደዚህ አይደሉም፡፡ በመጀመሪያ ደረጃ የቬዲክ እቀቀት የተገለፀው በጌታ ብራህማ ልብ ውስጥ ነው፡፡ ጌታ ብራህማም በመጀመሪያ ደረጃ የተፈጠረው ፍጥረት ነው፡፡ ብራህማም በተራው ይህንን እውቀት ለልጆቹ እና ለተማሪዎቹ አስተላለፈ፡፡ ይህም መልእክት የቀረበው ልክ በዓብዩ ጌታ እደቀረበው ተደርጐ ነው፡፡