AM/Prabhupada 1073 - በቁሳዊው ዓለም ውስጥ ያለው ብህርያችን ሁልግዜ ጌታ ለመሆን የምናደርገው ጥረት ነው፡፡



660219-20 - Lecture BG Introduction - New York

በ15ኛው የብሀገቨድ ጊታ ምዕራፍ ውስጥ የቁሳዊው ዓለም ፍጥረት ምን እንደሆነ በትክክል ተገልጾልናል፡፡ እንዲህም ተብሎ ተገልጿል “ኡርድህቫ ሙላም አድሀህ ሻክሀም አሽቫትሀም ፕራሁር አቭያያም” “ቻንዳምሲ ያስያ ፓርናኒ ያስ ታም ቬዳ ሳ ቬዳ ቪት” (ብጊ፡ 15.1) ይህም የቁሳዊው ዓለም ምን እንደሆነ የተገለፀው በ15ኛው የብሀገቨድ ጊታ ምዕራፍ ውስጥ ነው፡፡ ይህም ልክ ስሩ ወደ ላይ የሚታይ ዛፍ ተመስሎ ነው፡፡ “ኡርድህቫ ሙላም” ስሩ ወደ ላይ የሚታይ ዛፍ ዓይታችሁ ታውቃላችሁን? በእርግጥ ውሀ ውስጥ የተንፀባረቀ ዛፍ ስሩ ወደ ላይ ሆኖ እንደሚታይ ልምዱ አለን፡፡ ይህም በወንዝ አጠገብ ወይንም በኩሬ አጠገብ ሆነን ዛፉን ብናየው የተገላቢጦሽ ሆኖ ይታያል፡፡ ይህም ዛፍ በኩሬው ውሀ ውስጥ የሚታየው ቅርንጫፉ ተዘቅዝቆ እና ስሩ ወደ ላይ ሆኖ ነው፡፡ እንደዚሁም ሁሉ ይህ የቁሳዊው ዓለም ከመንፈሳዊው ዓለም ተንፀባርቆ የሚታይ ዓለም ነው፡፡ ይህም ልክ በውሀው ውስጥ ተንፀባርቆ እና የተገላቢጦሽ ሆኖ እንደሚታየው ዛፍ ነው፡፡ እንደዚህም ሁሉ ይህ የቁሳዊው ዓለም እንደ ጥላ ይመሰላል፡፡ እንደ የመንፈሳዊው ዓለም ጥላ ሆኖ ይመሰላል፡፡ ለምሳሌ በጥላ ውስጥ ምንም ቁሳዊ እና ሀቅ የሆነ ነገር የለም፡፡ ቢሆንም ግን ጥላው በእርግጥ እንዳለ እና እንደሚታይ ግልጽ የሆነ ነገር ነው፡፡ ሌላው ምሳሌ በበረሀ ውስጥ በርቀት እንደሚታየው ውሀ ነው፡፡ ይህም የሚያስመስለን ምንም እንኳን በበረሀ ውስጥ ውሀ ባይኖርም በርቀት ሲታይ ውሀ ያለ ያስመስለናል፡፡ እንደዚህም ሁሉ በዚህ በመንፈሳዊ ዓለም ጥላ ወይንም በቁሳዊው ዓለም ውስጥ ምንም ዓይነት ደስታ አይገኝም፡፡ ይህም የሚመሰለው ልክ በበረሀ ውስጥ እንደሚታየው ውሀ ነው፡፡ ቢሆንም ግን እርግጠኛው ውሀ ወይንም ትክክለኛው ደስታ የሚገኘው በመንፈሳዊው ዓለም ውስጥ ብቻ ነው፡፡ ዓብዩ ጌታ ወደ እዚሁ ወደ መንፈሳዊው ዓለም እንዴት ለመድረስ እንደምንችል ገልጾልናል፡፡ “ኒርማና ሞሀ” “ኒርማና ሞሀ ጂታ ሳንጋ ዶሳ አድህያትማ ኒትያ ቪኒቭርታ ካማህ” “ድቫንድቬር ቪሙክታ ሱክሀ ዱክሀ ሳምግኔር ጋቻንቲ አሙድሀህ ፓዳም አቭያያም ታት” (ብጊ፡ 15.5)

ይህም “ፓዳም አቭያያም” ወይንም የዘለዓለማዊው ቤተ መንግስት በአንድ “ኒርማና ሞሀ” በሆነ ሰው ሊደረስበት ይቻላል፡፡ (ከሹመት ፍላጎት ነፃ የሆነ) “ኒርማና ሞሀ” ኒርማና ማለት ሹመትን ወይንም ጌታ ለመሆን የሚፈልግ ማለት ነው፡፡ በአርቲፊሻል መንገድ ሹመትን እንሻለን፡፡ አንድ ሰው አቶ መሆን ይፈልጋል፡፡ ሌላው ደግሞ ጌታ መሆን ይፈልጋል፡፡ ሌላው ደግሞ ፕሬዚደንት ለመሆን ይፈልጋል፡፡ ሌላው ሀብታም መሆን ይፈልጋል፡፡ ሌላው ንጉስ ለመሆን ይፈልጋል፡፡ ለእነዚህ ማእረጎች ሁሉ ፍላጎት አለን፡፡ ቢሆንም ግን ለእነዚህ ማእረጎች ፍላጎት እሳካለን ድረስ ወደ መንፈሳዊው ዓለም መጓዝ አንችልም፡፡ ምክንያቱም እነዚህ ሁሉ ማእረጐች የሚገባቸው ለቁሳዊው ገላችን ነው፡፡ ነፍስ ግን ቁሳዊ ገላ አይደለችም፡፡ የመንፈሳዊው ዓለም መሰረታዊው እውቀት ይህ ነው፡፡ አንድ ሰው ለማንም አይነት ዓለማዊ ማእረግ መጓጓት የለበትም፡፡ “ጂታ ሳንጋ ዶሳ፣ ሳንጋ ዶሳ” በአሁኑ ግዜ ወደሶስቱ የቁሳዊው ዓለም ባህርዮች በጣም ቀርበን እንገኛለን፡፡ ከእነዚህም ዓለማዊ ብህርዮች በትሁት መንፈሳዊ አገልግሎት መላቀቅ እንችላለን፡፡ ወደ ትሁት የጌታ የመንፈሳዊ አገልግሎት የማንሰማራ ከሆንን እና ጉጉቱም ካላደረብን ከእነዚህ ከሶስቱ የዓለማዊ ባህርዮች መላቀቅ አንችልም፡፡ ስለዚህ አብዩ ጌታ እንዲህ ብሎናል “ቪኒቭርታ ካማህ” እነዚህ የሹመት እና ለቁሳዊ ነገሮች ጉጉት ያለን ለዓለማዊ ነገሮች የጋለ ፍላጎት ስላለን ነው፡፡ የቁሳዊው ዓለም ጌታ የመሆን የጋለ ፍላጐት አለን፡፡ ይህንንም የቁሳዊው ዓለም ጌታ የመሆን ጉጉታችንን እስካላስወገድን ድረስ ይህ ደረጃ ላይ እስክንደርስ ድረስ ወደ “ሳናታን ድሀማ” ወይንም ወደ ዓብዩ ጌታ ታላቁ ቤተ መንግስት ለመሄድ አንችልም፡፡ “ድቫንድቬር ቪሙክታሀ ሱክሀ ዱክሀ ሳምግኔር ጋቻንቲ አሙድሀህ አሙድሀህ ፓዳም አቭያያም ታት (ብጊ፡ 15.5) ይህም መንፈሳዊው ዓለም እንደዚህ ቁሳዊ ዓለም ግዜው ሲደርስ የሚደመሰስ ሳይሆን ዘለዓለማዊ ነው፡፡ ይህም መንፈሳዊ ዓለም በአሙድሀ ወይንም አስተሳሰቡ ግራ ባልተጋባ ሰው ሊደረስበት ይችላል፡፡ ይህም ሰው በዚህ ቁሳዊ ዓለም ጉጉት እና ሀሰተኛ ደስታ ያልተማረከ ነው ማለት ነው፡፡ በዓብዩ ጌታ የትሁት መንፈሳዊ አገልግሎት ላይ የተሰማራ ሁሉ ወደ እዚህ መንፈሳዊ ዓለም ለመሄድ ይችላል፡፡ ይህንንም ዘለዓለማዊ ቤተመንግስት ሊደርስበት የሚችለው ይህንን የመሰለው መንፈሳዊው እና ትክክለኛው ሰው ነው፡፡ ይህም ዘለዓለማዊው መንፈሳዊ ዓለም እንደ ቁሳዊው ዓለም ፀሀይ፣ ጨረቃ ወይንም የኤሌክትሪክ መብራት የሚያስፈልገው አይደለም፡፡ ይህ መልእክት እንዴት ወደ ዘለዓለማዊው ቤተመንግስት ለመሄድ እንደምንችል ትንሽ መንገዱን ያሳየናል፡፡