AM/Prabhupada 0034 - እያንዳንዱ ሰው እውቀት የሚያገኘው ከባለሥልጣን ነው፡፡

The printable version is no longer supported and may have rendering errors. Please update your browser bookmarks and please use the default browser print function instead.


Lecture on BG 7.1 -- Durban, October 9, 1975

ምእራፍ ሰባት:“ፍጹም የሆነ እውቀት” ሁለት አይነቶች እውቀት ይገኛሉ:ፍጹም የሆነ እውቀት እና አሻሚ የሆኑ እውቀቶች ይገኛሉ: ይህ አለም አሻሚ የሆነ እውቀት የሞላበት ነው:እዚህ አለም ላይም:አንዱን ነገር በደንብ ሳንረዳ ሌላውን ለመረዳት አንችልም: ”ይህ ልጅ ነው“ ብለን ስንል:አባትም እንደ አለ መረዳት አለብን: ”ይህ ባል ነው“ ብለንም ስንል:ሚስት መኖሯን መረዳት አለብን: ”ይህ ሰራተኛ ነው“ ብለንም ስንል: አለቃ መኖሩን መረዳት አለብን: ”እዚህ ብርሃን አለ“ ስንልም: ጨለማ እንደ አለ መረዳት አለብን: ይህም ብዙ የሚያሻሙ ነገሮች እንዳሉ ያሳየናል: አንዳንድ ነገሮችን ልንረዳችው የምንችው ከሚሻሙ ሃሳቦች ጋራ ነው: ቢሆ ንም ግን ሌላ ፍጹም የሆነ አለም አለ: እዚህም ፍጹም በሆነው መንፈሳዊ አለም ላይ:አገልጋዩ እና አለቃው በአንድ ደረጃ ላይ ይገኛሉ: ምንም እንኳን አነዱ የበላይ (ፈጣሪ)ሌላው አገልጋይ ቢሆንም:ደረጃቸው በአንድ መስመር ላይ ሁኖ ይሰማል የብሃጋቫድ ጊታም ሰባተኛ ምእራፍ: ሰለዚህ ሰለ ፍጹም ስለሆነ መፍፈሳዊ አለም:ትንሽ ትንተና ይሰጠናል: ይህ እውቀትም እንዴት እንደሚገኝ:ፍጹም በሆነው በጌታ ክርሽና ተነግሯል: ጌታ ክርሽና ፍጹም የሆነ የበላይ ሰው ነው: “ኢስቫራ ፓራማ ክርሽና ሳት ቺት አናንዳ ቭግረሃ:አናዲር አዲር ጎቪንዳ ሳርቫ ካራና ካራናም” (ብሰ 5 1) ይህም ስለ ክርሽና ገለጻ የተሰጠው: በጌታ ብራህማ በተጻፈው መጽሃፍ “ብራህማ ሰሚታ” በሚባለው ነው: ይህ መጽሃፍ የተገኘው: ከደቡብ ህንድ: በጌታ ቼይታንያ ነው: ከደቡብ ህንድም ጉዞው ሲመለስ: ለአገልጋዮቹ አቀረበላቸው: ስለዚህም ይህንን መጽሃፍ እንደ ዋና ስልጣን እንዳለው ተረድተን እንመራበታለን: ይህ ነው የእኛ የእውቀት መሰብሰቢያ ስልት: ስልጣን ያላቸውን ቅዱስ መፃህፍቶች እንከተላለን: ሁሉም ሰው እውቀት የሚያገኘው:ስልጣን ካለው ነው: ይህም ጠቅላይ ከሆነ ባለስልጣን ነው: የኛ ባለስልጣን አቀባበል ግን ትንሽ ለየት ይላል: በእኛ መመሪያ መሰረት: እኛ አንድ ባለስልጣን ከተቀበልን: የተቀበልነውም ባለስልጣን ደግሞ:ሌላ የራሱ ባለስልጣን ይኖረዋል: በእራስ የተሾመ ባለስልጣን አይኖረንም:: ይህም መሆን አይችልም:: ከሆነም እንከን የጎደለው ባለስልጣን ይሆናል:: ይህን ምሳሌ ብዙ ግዜ ሰጥቻለሁ:: ልጅ ከአባቱ ይማራል:: ልጅ አባቱን ይጠይቃል:: "አባቴ ይህ ማሽን ምንድን ነው?" አባቱም እንዲህ ይላል "ውድ ልጄ: ይህ ማይክራፎን ይባላል" እንደዚህም ሁሉ ልጅ ከአባቱ እውቀት ይወስዳል:: "ይህ ማይክራፎን ነው" እንደዚሁም ልጁ ለሌላ ሰው "ይህ ማይክራፎን ነው" ብሎ ከነታገረ: መልእክቱ ትክክል ነው:: ምንም እንኳን ትንሽ ልጅ ቢሆንም: የተቀበለው እውቀት ስልጣን ካለው ሰው ስለሆነ: የሚሰጠው ገለፃ ትክክል ነው:: እንደዚህም ሁሉ: የምንቀበለው እውቀት: ከትክክለኛ ባለ ስልጣን ከሆነ: ምንም እንደ ልጅ ብንሆንም: የምንሰጠው ገለፃ ትክክል ይሆናል:: ይህ ነው የእኛ እውቀት መሰብሰቢያ መንገድ: እኛ እውቀትን እራሳችን አንፈጥርም: ይህ ነው በ4 ኛ ምእራፍ ብሃጋቫድ ጊታ ውስጥ የተሰጠው መመሪያ: “ኤቫም ፓራምፓራም ፕራፕታም ኢማም ራጃርሻዮ ቪድሁ” (ብጊ 4 2) ይህ የፓራምፓራ ሲስተም ይባላል: “ኢማም ቪቫሽቫቴ ዮጋም ፕሮክታቫን አሃም አቭያያም ቪቫስቫን ማናቬ ፕራሃ ማኑር ኢክስቫካቬ ብራቪት” (ብጊ 4 1 ) “ኢቫም ፓራምፓራ” ስለዚህ ፍጹም የሆነ እውቀት ሊገኝ የሚችለው ግን: ፍጹም ከሆነ ሰው ስንሰማ ብቻ ነው: ከዚህ አለም ላይ ማንም ሰው ስለ ፍጹም ሰለሆነው እውቀት ከእራሱ አንደበት ፈጥሮ ሊነግረን አይችልም: ይህ የማይቻል ነው: እና እዚህ ስለ ፍጹም ስለሆነው አለም እንማራለን: ፍጹም የሆነ እውቀት:የፈለቀውም ፍጹም ከሆነው ከፍተኛው አምላክ: ፍጹም ከሆነው ሰው:ነው ፍጹም ሰው ማለትL ”አናዲር አዲር ጎቪንዳሃ“(ብሰ 5 1 ) እርሱም ዋራ የመጀመሪያ ሰው ነው:ሌላ መነሻ የለውም:ስለዚህም ፍጹም ይባላል: ፈጣሪ ማለትም በሌላ ሰው ወይንም ፍጥረት ያልተፈጠረ ማለት ነው: ይህም ፈጣሪ አምላክ ነው: ስለዚህም በዚህ ምእራፍ: እንዲህ ብሎ ተገልጿል:”ሽሪ ብሃገቫን ኡቫቻ“ ፍጹም የሆነ ሰው: ”ብሃጋቫን“ ማለት: በሌላ ሰው የማይተማመን ፍጹም ሰው ማለት ነው: