AM/Prabhupada 0355 - የምንገረው ነገር ሁሉ አብዮታዊ ለውጥ የሚያመጣ ነው፡፡

The printable version is no longer supported and may have rendering errors. Please update your browser bookmarks and please use the default browser print function instead.


Lecture on SB 5.5.1-8 -- Stockholm, September 8, 1973

”ካማን“ ማለት በህይወት የሚያስፈልጉን ነገሮች ሁሉ ማለት ነው የሚያስፈልጋችሁንም ነገር ሁሉ በቀላሉ ማግኘት ትችላላችሁ: መሬት በማረስ:እህል ይገኛል:ከላም ወተት ይገኛል: ይህ ነው:ይህ በቂ ነው: ነገር ግን መሪዎቹ ፕላን እያደረጉልን ነው:በግብርናቸው ከተደሰቱ ማን በፋክተሪ ውስጥ ይሰራል:ብለው ያስባሉ: ትንሽ እህል እና ወተት ካገኙ:ማን ፋክተሪ ውስጥ ይሰራል? ስለዚህም ታክስ ያደርጋሉ:እንደዚህም ቀላል ኑሮ መኖር ያዳግታል:ይህ ነው ሁኔታው: ኑሮን ለማቅለል ብትፈልጉም:የግዜው መሪዎች አይፈቅዱላችሁም: እንደ ውሻ:አሳማ እና አህያ:እንድትሰሩ ይመኛሉ:ይህ ነው ሁኔታው: ቢሆንም ከዚህ አሰፈላጊ ጥረት ግረት መራቅ አለብን: መንግስት እኔ ላይ እርምጃ ሊወስድ ይችላል እንደዚህም ስለተናገርኩ:ይህም አብዮታዊ አነጋገር ነው: አዎን:ግን ይህ እውነት ነው:አንድ ሰው ለምን ጥረት ግረት ውስጥ ይገባል? አምላክ ለሁሉም አቅርቧል:ለወፎች:ለአውሬዎች:ለእንስሳዎች:ለጉንዳኖች:እኔስ ለእርሱ አገልጋይ ከሆንሁኝ:ለምንድን ነው እህል የማይሰጠኝ? ምን ስህተት ሰራሁ?ስለዚህ በዚህ ሃሳብ አትረበሹ: የሚያስፈለጋችሁን ነገር በሙሉ:አምላክ ያቀርብላችኋል:ከእናንተ የሚጠበቅባችሁ ግን:ስለ ክርሽና ንቃታችሁ ወስናችሁ ወደ ፊት መራመድ አለባችሁ: በዚህ ሰሜት በማይሰጥ እምነት አትረበሹ:አመሰግናለሁ: