AM/Prabhupada 0047 - ክርሽና ፍፁም ነው፡፡



Lecture on BG 7.1 -- Upsala University Stockholm, September 8, 1973

የተለያዩ የዮጋ ስርዓቶች ይገኛሉ፡፡ እነዚህም ብሀክቲ ዮጋ፣ ግያና ዮጋ፣ ካርማ ዮጋ፣ ሃትሀ ዮጋ፣ ድህያና ዮጋ፣ ወዘተ ይባላሉ፡፡ ብዙ የዮጋ ስርዓቶች ይገኛሉ፡፡ ከሁሉም በላይ የሆነው ግን ብሀክቲ ዮጋ ተብሎ የሚታወቀው ነው፡፡ ይህም በመጨረሻው ምእራፍ ላይ ተገልፆ ይገኛል፡፡ አሁን የማነብላችሁ ግን የሰባተኛውን ምእራፍ ነው፡፡ በስድስተኛውም ምእራፍ ላይ ክርሽና እንዲህ ይላል፡፡ ዮጊናም አፒ ሳርቬሻም ማድ ጋቴናንታር አትማና ሽራድሃቫን ብሀጃቴ ዮማም ሳሜ ዩክታታሞ ማታሀ (ብጊ፡ 6.47) "ዮጊናም አፒ ሳርቬሻም" አንድ የዮጋ ስርዓትን የሚከታተል ሰው ዮጊ ይባላል፡፡ ክርሽናም እንዲህ ብሏል፡፡ "ዮጊናም አፒ ሳርቬሻም" ከዮጊዎች ሁሉ በላይ ቀደም ብዬ እንደጠቀስኩትም ብዙ የተለያዪ ዮጊዎች አሉ፡፡ "ከዮጊዎችም ሁሉ" "ዮጊናም አፒ ሳርቬሳም" ሳርቬሳም ማለት "ከሁሉም ዮጊዎች በላይ" ማለት ነው፡፡ ማድ ጋቴናንታር አትማና "በልቡ ውስጥ ሁሌ የሚያስታውሰኝ ሰው ሁሉ" ብሏል፡፡ ስለ ክርሽና ሁሌ ማሰብ እንችላለን፡፡ የክርሽናን ቅርጽ ውይንም ምስል ዓይተናል፡; የክርሽናን ሙርቲ እንሰግድለታለን፡፡ ይህንንም የክርሽና ሙርቲ ወይንም የክርሽናን ምስል የምንሰግድለት የክርሽና ምስል ከክርሽና ያልተለየ በመሆኑ ነው ፡፡ ቢሆንም ግን ይህንን ሙርቲ የማናገኝ ከሆነ የክርሽናን ቅዱስ ስም መዘመር እንችላለን፡፡ ይህም ቅዱስ ስም ከክርሽና ፈጽሞ የተለየ አይደለም፡፡

“አብሂናትቫን አትማ ናሚኖህ” (ቼቻ፡ ማድህያ 17.133) ክርሽና ፍፁም የሆነ ዓብይ ጌታ ነው፡፡ ፍፁምም በመሆኑ በእራሱ እና በስሙ መሀከል ምንም ዓይነት ልዩነት አናገኝም፡፡ እንደዚሁም ሁሉ በእራሱ እና በምስሉ መሀከል ምንም ዓይነት ልዩነት የለም፡፡ እንደዚህም ሁሉ በራሱ እና በስእሉ መሀከል ምንም ዓይነት ልዩነት አናገኝም፡፡ እንደዚህም ሁሉ በራሱ እና በታሪኩ ርእሶች መሀከል ምንም ዓይነት ልዩነት አናገኝም፡፡ ከክርሽና ጋር የተያያዙ ነገሮች ሁሉ ክርሽና ራሱ ናቸው፡፡ ይህንንም መረዳት ፍፁም የሆነ እውቀት ነው፡፡ ስለዚህ የክርሽናን ቅዱስ ስም ብተዘምሩ ወይንም የክርሽናን ምስል ብትሰግዱለት ሁሉም ነገር ክርሽና ራሱ ሆኖ ታገኙታላችሁ፡፡ ስለዚህ የመንፈሳዊ ትሁት አገልግሎቶች ሁሉ በተለያዩ መንገዶች ቀርበው ይገኛሉ፡፡ ሽራቫናም፣ ኪርታናም፣ ቪሽኑ ስማራናም፣ ፓዳ ሴቫናም፣ አርቸናም፣ ቫንዳናም፣ ዳስያም፣ ሳክያም፣ አትማ ኒቬዳናም (ሽብ፡ 7.5.23) ስለ ክርሽና ብቻ አዳምጡ፡፡ ይህም ማዳመጥ እራሱ ክርሽና ነው፡፡ ለምሳሌ በአሁኑ ሰዓት ስለክርሽና እያዳመጥን እንገኛለን፡፡ ይህም ማዳመጥ እራሱ ክርሽና ነው፡፡ እነዚህ ልጆች እና ልጃገረዶች በመዘመር ላይ ይገኛሉ፡፡ ይህም መዘመር እራሱ ክርሽና ነው፡፡ “ሽራቫናም ኪርታናም” ከዚያም በኋላ “ስማራናም” ስለ ክርሽና ስንዘምርም ሆነ የክርሽናን ምስል ብናስታውስ ይህም እራሱ ክርሽና ነው፡፡ የክርሽናንም ስእል ስናይ ይህም እራሱ ክርሽና ነው፡፡ የክርሽናንም ሙርቲ ስናይ ይህም እራሱ ክርሽና ነው፡፡ ስለ ክርሽና ትምህርት ስንወስድም ይህም ራሱ ክርሽና ነው፡፡ ስለዚህም በሁሉም መንገድ

“ሽራቨናም፣ ኪርታናም፣ ቪሽኑ ስማራናም፣ ፓዳ ሴቫናም፣ አርቸናም፣ ቫንዳናም፣ ዳስያም፣ ሳክያም፣ አትማ ኒቬዳናም” (ሽብ፡ 7.5.23) ከእነዚህም ከዘጠኝ ስርዓቶች አንዱን እንኳን ብትከተሉ ወይንም ብትቀበሉ ወዲያውኑ ከክርሽና ጋር መገናኘት ትችላላችሁ፡፡ ከተቻለ ዘጠኙንም መከተል፣ ወይንም ስምንቱን፣ ወይንም ሰባቱን፣ ወይንም ስድስቱን ወይንም አምስቱን፣ አራቱን፣ ሶስቱን፣ ሁለቱን ወይንም አንዱን ብቻ እንኳን ብትከተሉ ወይንም በጥሞና ብተከታተሉ ሕይወታችሁ የተሳካ ይሆናል፡፡ ለምሳሌ ይህ በህብረት መዘመር ምንም ወጪ አያስወጣንም፡፡ በመላው ዓለምም ላይ በመዘመር ላይ እንገኛለን፡፡ እኛንም በማዳመጥ ማናቸውም ሰው መዘመር ይችላል፡፡ ምንም ዓይነት ወጪ የማያስወጣችሁ ነው፡፡ ብትዘምሩም የሚጎልባችሁ ነገር አይኖርም፡፡ ይህንንም ብታደርጉ ከክርሽና ጋር በቀላሉ ለመቀራረብ ትችላላችሁ፡፡ ይህም ወዲያውኑ በመሆኑ ትልቅ ጥቅም ያለው ስርዓት ነው፡፡ ምክንያቱም የክርሽና ስም እና ክርሽና ራሱ ልዩነት ስለሌላቸው ነው፡፡ “አብሂናትቫን ናማ ናሚኖህ” (ቼቻ፡ ማድህያ 17.133) እነዚህም የቬዲክ መፃህፍቶች ገለፃ ናቸው፡፡ “አብሂናትቫን ናማ ማሚኖህ ናማ ቺንታማኒህ ክርሽና” የክርሽና ስም “ቺንታመኒ” ተብሎ ይታወቃል፡፡ ቺንታመኒ ማለት መንፈሳዊ ማለት ነው፡፡ “ቺንታመኒ ፕራካራ ሳድማሱ ካልፓ ቭርክሻ ላክሻቭርቴሹ” (ብሰ፡ 5፡29) እነዚህ የቬዲክ ገለፃዎች ናቸው፡፡ ክርሽና የሚኖርበት ቦታ በደንብ ተገልጿል፡፡ “ቺንታመኒ ፕራካራ ሳድማሱ ካልፓ ቭርክሻ ላክሻቭርቴሹ ሱራብሂር አብሂፓላያንታም” (ብሰ፡ 5፡29) ስለዚህ “ናማ” ወይንም የሽሪ ክርሽና ቅዱስ ስም እራሱ “ቺንታመኒ” ወይንም መንፈሳዊ ነው፡፡ “ናማ ቺንታመኒ ክርሽና” ይህም ቅዱስ ስም ክርሽና እራሱ ነው፡፡ “ናማ ቺንታመኒ ክርሽና ቼታንያ” (ቼቻ፡ ማድህያ 17.133) “ቼይታንያ” ማለት ያልሞተ ወይንም ነዋሪ ፍጥረት ማለት ነው፡፡ የክርሽናን ስም በመዘመር ልክ ከክርሽና ጋር በቀጥታ እንደምትነጋገሩት የሆነ ጥቅም ታገኙበታላችሁ፡፡ ይህም የሚቻል ነገር ሲሆን ይህንንም በትክክል ልንረዳ የምንችለው ግን ከግዜ በኋላ ነው፡፡ “ናማ ቺንታመኒ ክርሽና ቼይይታንያ ራሳ ቪግራሀ” “ራሳ ቪግራሀ” ማለት ደስታ ማለት ነው፡፡ ወይንም የደስታ ሀይቅ ማለት ነው፡፡ ይህንን የሀሬ ክርሽናን ቅዱስ ስም ስትዘምሩ መንፈሳዊ የሆነ ደስታ ቀስ በቀስ እያገኛችሁ ትመጣላችሁ፡፡ ልክ እንደነዚህ ልጆች እና ልጃገረዶች፡፡ በመዘመር ላይ እያሉ በመደነስ ደስታን ሲያገኙ ይታያሉ፡፡ ማንም ሊረዳቸው አይችል ይሆናል፡፡ ነገር ግን በመዘመራቸው በእብደት የተሰመጡ አይደሉም፡፡ ነገር ግን በመዘመራቸው መንፈሳዊ ደስታን እያገኙ ይገኛሉ፡፡ ስለዚህም ሲደንሱ ይታያሉ፡፡ ውሻ ሲደንስ አናየውም፡፡ ይህ መደነስ ግን መንፈሳዊ ዳንስ ነው፡፡ ነፍስ እየደነሰች ነው፡፡ ስለዚህም ሽሪ ክርሽና “ራሳ ቪግራሀ” ወይንም የደስታ ሁሉ ሀይቅ ተብሎ ይታወቃል፡፡

“ናማ ቺንታማኒ ክርሽና ቼይታንያ ራሳ ቪግራሀ ፑርናህ” (ቼቻ፡ ማድህያ 17.133) “ፑርና” ማለት የተሟላ ማለት ነው፡፡ 1 ከመቶ የጎደለው ማለት አይደለም፡፡ ፑርናም ማለት መቶ በመቶ ማለት ነው፡፡ የተሟላ፡፡ “ፑርና” ማለት የተሟላ ማለት ነው፡፡ “ፑርናሀ ሹድሀ” ሹድሀ ማለት የፀዳ ማለት ነው፡፡ በዚህ ቁሳዊ ዓለም ውስጥ ብዙ የተበከሉ ነገሮች ይገኛሉ፡፡ ቁሳዊ የሆነ ስም ሁሉ የተበከለ ነው፡፡ ይህንንም ቁሳዊ ስም በተደጋጋሚ በመዘመር ለብዙ ጊዜ ለመቀጠል አትችሉም፡፡ ይህም የተለየ ሙከራ ነው፡፡ ቢሆንም ግን ይህንን የሀሬ ክርሽና ቅዱስ ስም ወይንም ማንትራ ብትዘምሩ ምንም እንኳን ለ24 ሰዓትም ብትዘምሩ ምንም ልትደክሙ ወይንም ልትሰለቹ አትችሉም፡፡ ይህ ነው ሙከራው፡፡ መዘመሩን ቀጥሉበት፡፡ እነዚህ ልጆች ለ24 ሰዓት መዘመር ይችላሉ፡፡ ይህም ያለ ምግብ እና ውሀ ሊሆን ይችላል፡፡ ደስታንም የሚሰጥ ዝማሬ ነው፡፡ ምክንያቱም የተሟላ በመሆኑ ነው፡፡ መንፈሳዊ ወይንም የፀዳ “ሹድሀ” በመሆኑ ነው፡፡ “ሹድሀ” ማለት ንፁህ ማለት ነው፡፡ በቁሳዊ ዓለም ያልተበከለ ማለት ነው፡፡ ከሁሉም ዓይነት ደስተኛ ነገሮች ሁሉ የቁሳዊው ዓለም ከፍተኛው ደስታ የወሲብ ግኑኝነት ነው፡፡ ቢሆንም ግን ይህንን የወሲብ ደስታ ለ24 ሰዓት ልትደሰቱበት አትችሉም፡፡ ለጥቂት ደቂቃዎች ልትደሰቱበት ትችሉ ይሆናል፡፡ ይኅው ነው፡፡ ተገዳችሁ እንድትደሰቱበት ብትጠየቁ እንኳን አሻፈረኝ በማለት እምቢ ለማለት ትበቃላችሁ፡፡ “አልፈልግም!” ይህ የቁሳዊው ዓለም የተበከለ ደስታ ሲሆን የመንፈሳዊ ደስታ ግን ወሰን የለውም፡፡ ይህንንም የመንፈሳዊ ደስታ ያለማቋረጥ ለ24 ሰዓትም ቢሆን ልትቀጥሉበት ትችላላችሁ፡፡ ይህ የመንፈሳዊ ደስታ ይባላል፡፡ “ብራህማ ሶክህያም አናንታም” (ሽብ፡ 5.5.1) አናንታም፡፡ አናንታም ማለት ወሰን የሌለው ወይንም የማያልቅ ማለት ነው፡፡