AM/Prabhupada 0005 - ስለ ፕራብሁፓድ ሕይወት በሶስት ደቂቃ ውስጥ፡፡

The printable version is no longer supported and may have rendering errors. Please update your browser bookmarks and please use the default browser print function instead.


Interview -- September 24, 1968, Seattle

ቃለ መጠይቅ: ስለ እራስዎ የህይወት ታሪክ በአጭሩ ሊነግሩን ይችላሉ? የት ትምህርትዎን እንደተማሩ እና እንዴት የጌታ ክርሸና አገልጋይ ለመሆን እንደበቁ: ቢነግሩን:: ፕራብሁፓዳ: ትውልዴ እና ትምህርት ያጠናቀቅሁት በካልካታ ውስጥ ነው:: ካልካታ ቤቴ እና ያደግሁበት ቦታ ነው:: የተወለድሁትም እንደ አውሮፓውያን አቆጣጠር በ1896 ነው:: ከአባቴም በጣም ቀርቤ ያደግሁ ልጅ ነበርሁ:: ትምህርትም የጀመርሁት ትንሸ ረፈድ ካለ በኋላ ነበር:: በከፍተኛ ደረጃ ትምህርትቤትም ለ8 አመት ያህል ተማርኩ:: በፕራይመሪ ትምህርት ቤት ለ4 አመት: እንዲሁም በከፍተኛ ደረጃ 8 አመት ተማርኩ:: በኮሌጅ ውስጥ ደግሞ ለ4 አመት ተማርኩ:: ከዚያም በኋላ በአገ"የገራችን በነበረው "የጋንዲ" እንቅስቃሴ ውስጥ ገብቼ መሳተፍ ጀመርኩ:: ይሁን እንጂ በጥሩ አጋጣሚ ከመንፈሳዊ አስተማሪዬ ጋራ በ1922 ለመገናኘት በቃሁ:: ከዚያን ግዜ በኋላም በዚህ መስመር ለመከተል የፀና ስሜት አደረብኝ:: ቀስ በቀስ ከቤተሰብ ኑሮዬ ገለል ብዬ: ወደ እዚህ ለማተኮር በቃሁ:: ትዳር የያዝኩትም በ1918 የ3 ኛ አመት የኮሌጅ ተማሪ እያለሁ ነበር:: በዚን ግዜም ልጆች ለመያዝ በቃን:: ያን ግዜም ንግድ ጀምሬ ነበር:: በ 1954 ከትዳር እና ከቤተሰብ ኑሮዬ ገለል ብዬ ወደ መንፈሳዊ አለም ማተኮር ጀመርኩ:: ለ 4 አመት ያህልም ለብቻዬ ያለ ቤተሰቤ: ወደ እዚህ በማተኮር ኑሬአለሁ:: በ 1959 የመሎክሴ ኑሮም ለመኖር: በቤተ መቅደስ ውስጥ: ሥነ ሥርአቱን አጠናቀቅሁ:: ከዚያም ቅዱስ መጽሀፎችን ለመፃፍ ትኩረት አደረግሁ:: በመጀመሪያም የታተመው መፅሀፍም በ 1961 ነበር:: በዚያን ግዜም 3 መፅሀፍቶች ለማሳተም በቃሁ:: ከዚያም በ 1965 ለእናንተ አገር (በእንግሊዘኛ) ለማሳተም በቃሁ:: እዚህ (አሜሪካ) የገባሁትም በ1965 ነው:: ከዚያም በኋላም: የክርሸናን ንቃት ለማስተማር: በአሜሪካ: በካናዳ: እና በአውሮፓ ውስጥ: ለመዞር በቃሁ:: በዚህም መንገድ: ቅርንጫፎቻችን: ለመዳበር በቁ:: የተማሪዎቻችንም ቁጥርም እየጨመረ መጣ:: ወደፊትም ምን እንደሚከናወን ለማየት ያብቃን:: ቃለ መጠይቅ: እርስዎስ አገልጋይ ለመሆን እንዴት ለመሆን በቁ? አገልጋይ ከመሆንዎስ በፊት ምን ነበሩ: ምንስ ይከተሉ ነበር? ፕራብሁፓዳ: የምከተለውም እንደገለጽኩት የእምነት ኑሮ ነበር:: አንዱ የቅርብ ጓደኛዬም: ወደ መንፈሳዊ አስተማሪዬ: ለማስተዋወቅ: ጎትቶ ወስዶኝ ነበር:: ከመንፈሳዊ አስተማሪዬም ጋራም ለመጀመሪያ ግዜ ስተዋወቅ: በጣም እንድሳብ ለማድረግ አበቃኝ:: ከዚያም ግዜ ጀምሮ: የመንፈሳዊው ዘር መዳበር ጀመረ::