AM/Prabhupada 0009 - ትሁት የአምላክ አገልጋይ የሆነው ሌባ፡፡

The printable version is no longer supported and may have rendering errors. Please update your browser bookmarks and please use the default browser print function instead.


Lecture on SB 1.2.12 -- Los Angeles, August 15, 1972

ጌታ ክርሽና በብሃገቫድ ጊታ እንዲህ አለ:: [ብ ጊ 7 15] "ናሃምፕራካሻ ሳርቫስያ ዮጋ ማያ ሳማቭርታሃ" "እኔ ለሁሉም ግልጽ አይደለሁም:: "ዮጋ ማያ" ዮጋማያ ትሸፍነናለች:: ታድያ: እንዴት አማላክን ለማየት እንችላለን? ነገር ግን እነዚህ ተንኮለኞች አሉ:: እንደዚህም ይላሉ "አምላክን ልታሳየኝ ትችላለህ? አማላክን አይተኅው ታቃለህ?" አምላክ አሁን እንደ መጫወቻ ሁኖዋል:: "አማላክ ይኅውና:: ይህ የአምላክ ወልድ ነው" የሚል ይበዛል:: [ብ ጊ 7 15] "ና ማም ዱስክሪቲኖ ሙድሃህ ፕራፓድያንቴ ናራድሃማህ" እነዚህም ሀጥያተኞች: ተንኮለኞች: ሞኞች እና ከሰው ሁሉ ዝቅተኞች ናቸው እንዲህም እያሉ ይጠይቃሉ: “አማላክን ልታሰየኝ ትችላለህ?" ምን አይነት የተግባር ሥልጣኔ ቢኖርህ ነው: አማላክን ለይተህ አየተህ ለማወቅ የምትችለው? ለዚህ የሚያስፈልገው የተግባር ሥልጣኔ የሚከተለው ነው:: ይህስ ምንድን ነው? "ታክ ሸራዳድሃና ሙናያሃ" በመጀመሪያ ደረጃ: አንድ ሰው እምነት እንዲኖረው ያስፈልጋል:: እምነትኛ:: "ሽራዳድሃናህ" አማላክንም ለማየት በጣም ጉጉት ያለው ሰው መሆን አለበት:: እንዲሁ: ወደ አንድ ወገን በማዳላት እና: ቁም ነገር በሌለው ቀለድ: "እስቲ አማላክን አሳየኝ" ብሎ መጠየቅ አይገባም:: እንደ ማጂክ! አማላክ እንደ ማጂክ የሚፈጠር ይመስላቸዋል:: አይደለም:: አማላክን የሚሻ ሰው: በጣም ኮስተር ብሎ ለማየት መሻት አለበት:: እንዲህም ይላሉ: "አዎ: ማናልባት ፈጣሪ ካለ" "ስለ አማላክ ሰምተናል" "እና ማየት አለብን" ማለት አለብን:: ከዚህም የተያያዘ አንድ ታሪክ አለ:: ብትሰሙትም ጥሩ ምክር የያዘ ነው:: አንድ ባለ ሙያ የቅዱስ ብሃጋቫድ ጊታ ደጋሚ (አንባቢ) ነበር:: ሲያነብም: ጌታ ክርሽና በጣም በቆንጆ ጌጣ ጌጥ: አሸብርቆ እንደነበረ ያነብ ነበር:: እንደዚህም አሸብርቆ: ለላሞች እረኝነት ወደ ጫካ ይላክ ነበር:: ይህም ስለመሆኑ ሲነበብ አንድ የተረዳ ሌባ ነበረ:: ሌባውም እንዲህ ብሎ አሰበ:: "ለምን ወደ ቭርንዳቫን ሂጄ ይህንን ልጅ አልዘርፈውም?" "ብዙ ጌጣ ጌጥ ይዞ: በጫካ ውስጥ ይገኛል::" "እዚያም ሂጄ: ልጁን ይዤ: ጌማ ጌጡን ሁሉ መውሰድ እችላለሁ::" ፍላጎቱም ይሄ ነበር:: እንድዚሁም ሁኖ ልጁን ለማግኘት የፀና ሃሳብ አደረበት:: በዚህም መንገድ "በአንድ ሌሊት ሚሊዮኔር መሆን እችላለሁ" ብሎ አሰበ:: "ብዙ ጌጣጌጥ ይገኛል" ብሎ አስበ:: በዚህም ተነሳስቶ ጉዞውን ጀመረ:: ዋናው ጽኑ ሃሳቡም "ክርሽናን ማየት አለብኝ" የሚል ነበር:: "ክርሽናን ማየት አለብኝ" የሚለው የጸና ሃሳቡም: ጌታ ክርሽናን ለማየት እንዲበቃ አደረገው:: ጌታ ክርሽናንም ያገኘው ልክ ቅዱስ ብሃገቫት ውስጥ ደጋሚው እንደገለጸው ሁኖ ነው:: ልክ ክርሽናን እንደአየውም "ኦ ክርሽና አንተ በጣም ጥሩ ነህ" አለ:: እና ክርሽናን ማወደስም ጀመረ:: እንዲህም ብሎ አሰበ: "ቀስ በቀስ በማወደስ ጌጣጌጡን ሁሉ እወስዳለሁ" የመጣበትንም አላማ መግለጽ ጀመረ:: "አንተ ሃብታም ትመስላለህ: ትንሽ ጌጣጌጦችህን ልውሰድ?" ብሎ ጠየቀ:: ክርሽናም እንዲህ አለ: "አይሆንም: እናቴ በጣም ትቆጣለች: ስለዚህ አልችልም" ብሎ መለሰ:: ክርሽናም: በልጅነት አንደበት መለሰለት:: በዚህም ሁኔታ ሌባው: ወደ ክርሽና ያለው ጉጉት እያደገ መጣ:: በዚህም ወደ ክርሽና ባለው ቅርበቱ: ልቡ ንጹህ እየሆነ መጣ:: ከዚያም መጨረሻ ላይ: ክርሽና "እሺ መውሰድ ትችላለህ" አለው:: ከዚህም በኋላ: ሌባው ወደ ክርሽና አገልጋይነት ተቀየረ:: ይህም ወደ ክርሸና በመሰረተው ቅርበቱ ነው:: እንደዚህም ሁሉ በተገኘው መንገድ: ወደ ክርሽና ለመቅረብ መንገድ መፍጠር አለብን:: በተገኘው መንገድ:: በእንደዚህም ልባችን ንጹህ ሊሆን ይችላል::