AM/Prabhupada 0020 - ክርሽናን በትክክል መረዳት ቀላል ነገር አይደለም፡፡

The printable version is no longer supported and may have rendering errors. Please update your browser bookmarks and please use the default browser print function instead.


Arrival Lecture -- Miami, February 25, 1975

የጌታ ክርሽናን ማንነት ለመረዳት ቀላል አደለም: “ማኑስያናም ሳሃሽሬሹ ካሽቺድ ያያቲ ሲድሃዬ ያታታም አፒ ሲድሃናም ካሽቺድ ቬቲ ማም ታትቫታሃ (ብ ጊ 7 3) ከብዙ ሚሊዮን ህዝቦች መሃከል:አንዱ መንፈሳዊ ህይወቱን በደንብ ለማስተካከል ትሁት ልቦና ይኖረዋል: አለበላዛ ግን ሌሎች ምንም ፍላጎቱ የላቸውም: እንዲያውም የህይወታችን መሳካት በምን እንደተመሰረተም አያውቁም: በዚ በአሁኑ አለማዊ ስልጣኔ: ሁሉም እንዲህ ብሎ ያስባል: ”እኔ ጥሩ ሚስት ካገኘሁ:ጥሩመኪና ካገኘሁ እና ጥሩ ቤት ካገኘሁ:ህይወቴ የተሳካ ይሆናል“ ብሎ ያስባል: ይህ የህይወታችን መሳካት አይደለም: ይህ ግዜያዊ ነገር ነው: ትክክለኛው የህይወት መሳካት ግን:ከ ”ማያ“ (ዐለማዊ ኑሮ)ሠንሠለት መፈታት ነው: ይህም ከዚህ ዐለማዊ ኑሮ እስር:ከመወለድ:ከመሞት:ከማርጀት እና ከመታመም: መፈታት ማለት ነው: እኛ (ነፍሳችን) በተለያየ ህይወት እያለፍን እንገኛለን: ይህ የሰው ትውልዳችን ደግሞ: ከዚህ እስር ቤት እንድንወጣ የሚረዳን ጥሩ አጋጣሚ የሚሰጠን ህይወት ነው: ከእነዚህ ሁሉ የተለያየ ፍጥረት ኑሮአችን (ከትውልድ በፊት)የተለየ ነው ማለት ነው: ነፍስ ዘለአለማዊ እና ደስተኛ ናት: ይህም ምክንያቱ የአማላክ ቅንጣፊ አካል በመሆንዋ ነው: ”ሳት ቺት አናንዳ“ ነፍስ ዘለአለማዊ: ደስታኛ እና ሙሉ እውቀት ያላት ናት: ነገር ግን በዚህ አለማዊ ምድር ውስጥ ገብታ:የተለያየ ገላ ይዛ መኖር ጀምራለች: በዚህም ምክንያት መወለድ እና መሞት የሌለበት መንፈሳዊ ዐለም ውስጥ አይደለም ያለነው: ይህ ዐለም ድንቁርና ያለበት ነው: ከዚህ ቀደም አንድ ሳይካያትሪስት ሊያየኝ መጥቶ ነበር: ስለ ነፍስ ትምህርቱን እና ስለ ነፍስ ዋና መዋቅሩን ተንትኖ የተረዳው እንዴት ነው? እንደዚሁም መላ አለም በመንፈሳዊ አለም ድንቁርና ውስጥ ይገኛል: መላ የገለም ህዝብ ትኩረቱ:ለዚች ለ 50 ወይንም 60 ወይንም 100 አመት ርዝመት ላላት ህይወት ነው: ነገር ግን ነፍስ ዘላለማዊ መሆንዋን:ደስታኛ እና ዕውቀት የሞላት መሆንዋን ዘንግተዋል ይህን መወለድ መሞት ማርጀት እና መታመምን የምናየው:ነፍ ጊዝያዊ ገላ ውስጥ ገብታ በመወለዷ ብቻ ነው: ይህም ተደጋግሞ የሚከሰት ነው: በዚህም ምክንያት ጌታ ቼይታንያ በርህራሄው ይህንን ለማስተማር ወደዚህ አለም ላይ መጣ: ክርሽናም ወደ እዚህ አለም ይመጣል:ነገር ግን ወደ አገልጋዮቹ ያዘነብላል: ክርሽና መጀመሪያ ልቦናህን ስጠኝ:ከዚያም እኔ እደግፍሃለሁ ይላል: ነገር ግን:ጌታ ቼይታንያ እና ክርሽና አንድ ይሁኑ እንጂ:ጌታ ቼይታንያ ለሁሉም ርህራሄ ያለው ነው:(ለሃጥያተኛውም) ስለዚህም በጌታ ቼይታንያ በረከት ምክንያት:ጌታ ክርሽናን በደንብ ለመረዳት በቅተናል: ጌታ ቼይታንያ እዚህ በተመቅደስ ውስጥ አለ: ሰገዱለት: ምንም የሚያዳግት አይደለም: “ያግያ ሳንኪርታና ፕራዬር ያጃንቲ ሂ ሱ ሜድሃሳሃ” “ክርሽና ቫርናም ትቪሻ ክርሽናም ሳንጎፓንጋስትራ ፓርሳዳም:ያግና ሳንኪርታናም” (ሽ ብ 11 5 32) በቀላሉ የ “ሀሬ ክርሽናን” ቅዱስ ስም ዘምሩ: የቻላችሁትን ያህልም ለጌታ ቼይታንያ አቅርቡ: በጣም ርህሩህ ነው:ሃጥያታችንን ብቻ አይመለከትም ራድሃ ክርሽና ስግደት ግን ትንሽ ሊከብድ ይችላል: በትልቅ ክብር እና ሞገስ መስገድ ያስፈልገናል: ጌታ ቼይታንያ በዚህ አለም ላይ በፍቃዱ እኛን ለማዳን ነበር የመጣው: ትንሽም አገልግሎት ስንሰጠው በጣም ይደሰታል: ነገር ግን ማገልገሉን እንዳታቋርጡ: ገና ለገና አዛኝ እና ትሁት ስለሆነ: ማንነቱን መዘንጋት አለብን ማለት አይደለም: እርሱ ታላቁ ጌታ ፈጣርያችን ነው: እንደዚሁም ሁሉ ያለንን ሁሉ ትልቅ ክብር ለእርሱ መስጠት ይገባናል: ዋናው ጥቅማችን ጌታ ቼይታንያ ሃጥያታችንን አይቶ አይርቀንም: እርሱን ለማስደሰትም መስገዱ እና ማገልገሉ: ቀላል ነው: “ያግና ሳንኪርታናህ ፕራዬር ያጃንቲ ሂ ሱ ሜድሃሳሃ” በቀላሉ የ “ሀሬ ክርሽናን” ቅዱስ ስም በመዘመር ብቻ:ልታስደስቱት ትችላላችሁ: እርሱም ይህንን መዘመር እና መደነስን አስተምሮናል: ይህም አማላክን ለመረዳት እንድንችል የሚያደርግ ቀላሉ መንገድ ነው: በተቻለ መጠን መዘመር ነው: ከተቻለም 24 ሰዓት: ያ የማይቻል ከሆነ ደግሞ:ቢያንስ 4 ግዜ ወይንም 6 ግዜ: በጌታ ቼይታንያ ፊት ለፊትም ብትዘምሩ: ህይወታችሁ የተሳካ ይሆናል: ይህም የተረጋገጠ ነው: