AM/Prabhupada 0025 - ከልብ የመነጨ ነገር ለሰው ከሰጠን ሊሰራ ይችላል፡፡

The printable version is no longer supported and may have rendering errors. Please update your browser bookmarks and please use the default browser print function instead.


Conversation with Yogi Amrit Desai of Kripalu Ashram (PA USA) -- January 2, 1977, Bombay

ዮጊ አምርት ደሳይ: እንዲህ አለ “ለአንተ በጣፍ ፍቅር ስለአለኝ:አንተን ለማየት መጥቻለሁ” ብሎ ተናገረ: ፕራብሁፓዳም:አመሰግናለሁ አለ: ዮጊ አምርት ደሳይ:“አገልጋዮቹን ሁሉ እንዲህ እላቸው ነበር” ፕራብሁፓዳ: "ከዶክተር ሚሽራ ጋር ነህን?“ ዮጊ አምርት ደሳይ:”አይደለሁም: እዚህ ያሉትን አገልጋዮች እንዲህ እላቸው ነበር“ ”ለመጀመሪያ ግዜ ወደ ምእራባዊ አገሮች የብሃክቲን ትምህርት ያመጣው ሽሪላ ፕራብሁፓዳ ነው: ይህም በጣም አስፈላጊ ነበረ:“ ምክንያቱም እዚህ ብዙ ሃሳብ ጭንቅላት ውስጥ አለ:ማሰብ:ማሰብ:ማሰብ: ይህ የፈጣሪ ፍቅር በጣም ጥልቀት ያለው ነው: ፕራብሁፓዳ:”እየውልህ: ንጹህ እና ልክ የሆነ ነገር ካቀረብን:“ ዮጊ አምርት ደሳይ:”በጣም የታመነ“ ፕራብሁፓዳ: ”ሰው ሊረዳው እና ሊቀበለው ይችላል“ ዮጊ አምርት ደሳይ:”ለዚህም ነው ድርጅቱ በቆንጆ መንገድ እያደገ የሚገኘው:ምክንያቱም በጣም የታመነ ስለሆነ ነው:“ ፕራብሁፓዳ: ”ስለዚህም የእያንዳንድ ህንድ ሃላፊነት ይህንን የታመነ ትክክለኛ ትምህርት ለአለም መስጠት ነው“ ይህም ”ፓራ ኡፓካር“ ይባላል:”እኔም ከመምጣቴ በፊት ብዙ ስዋሚዎች እና ዮጊዎች ከህንድ መጥተው ሊያታልሏቸው ተሰማርተው ነበረ:“ ዮጊ አምርት ደሳይ:”አይደለም:እውነትን ለመስጠት ፈርተው ነው:ይህም ሰው ይቀበለናል ብለው ፈርተው ስለነበረ ነው:“ ፕራብሁፓዳ: ”እውነት ምን እንደሆነ አያውቁም: ፈርተው ግን አይደለም“ ለምን?አንድ ሰው እውነትን ከያዘ መፍራት የገባውናልን? ዮጊ አምርት ደሳይ:”እርግጥ ነው“ ፕራብሁፓዳ: “ከቪቬካናንዳ ጀምሮ:እውነት ምን እንደሆነ አያውቁም ነበረ:” ዮጊ አምርት ደሳይ:”ይህ ሙሉ በሙሉ ትክክል ነው: ይህንንም አንተ ከመጣህ በኋላ አይተነዋል“ እኔም በ1960 እዚያ ነበርኩ: ዮጋ ማስተማርም ጀምሬ ነበረ: ነገር ግን አንተ ከመጣህ በኋላ:ፍርሃቴ ጠፍቶ ብሃክቲ እና መቁጠሪያ ማስተማር ጀመርኩ: አሁን ብዙ የብሃክቲ ማስተማርያ ገዳሞች አሉን:ብዙ የብሃክቲ ይህንንም ክብር ለአንተ እሰጣለሁ ምክንያቱም በፊት ይህንን ለማስተማር እፈራ ነበር: እንዲህም አስብ ነበር ”እነዚህ ክርስቲያኖች ናቸው:ቡዙ የፍቅር አገልግሎትን መስጠት አይፈልጉ ይሆናል: ላይረዱትም ይችላሉ: ነገር ግን አንተ ተአምር ሰርተሃል:አማላክ ጌታችን ክርሽናም በአንተ በኩል ተአምር ሊሰራ በቅቷል: ይህንንም ትልቅ ተአምር በመሬት ላይ ማየት በጣም የሚያስገርም ነው: ይህም በጣም ጥብቅ ሁኖ ይሰማኛል: ፕራብሁፓዳ: “ይህንን ቃል መስጠትህ ሩህሩህነትህ ነው” “የታመነ ንጹህ ነገር ከሰጠን:ይህ ይሰራል:” ዮጊ አምርት ደሳይ:“በእርግጥ:ይህንን ነው እኔም ለማድረግ የምሞክረው:ሁላችንም:” 180 ሰዎች በገዳማችን ይኖራሉ:ሙሉክስናም እይተለማመዱ ነው: ጥዋትም በ 4 ኤ ኤም ተነስተው:በ 9 ፒ ኤም ይተኛሉ እርስ በእርስም አይነካኩም: በተለያየ ክፍልም ተኝተው ያድራሉ: ለመዘመር ሲቀመጡም ተለያይተው ነው:ሁሉም ነገር ጥብቅ ነው: አልኮል መጠጥ:ስጋ: ሻይ: ቡና:ነጭ ሽንሁርት:ቀይ ሽንኩርት ሁሉ አይፈቀድም:ንጹህ ኑሮ አላቸው: ፕራብሁፓዳ: “በጣም ጥሩ ነው: እኛም ይህን ሁሉ እንከተላለን” ዮጊ አምርት ደሳይ:“አዎን” ፕራብሁፓዳ: “ታድያ እናንተም ዴይቲ አላችሁ?” (የክርሽና ፎርም) ዮጊ አምርት ደሳይ:“አዎን ያለንም ዴይቲ የክርሽና እና የራድሃ ነው” የኔም ጉሩ ስዋሚ ክርፓሉ አናንዲ ይባላል: ባሮዳ ህንድ አገርም አንድ ገዳም አለው: በመንፈሳዊ አለም 27 አመት አገልግሏል:በፀጥታ ደግሞ 12 አመት ተቀምጧል: ባለፉት ሁለት አመታት ግን አንድ ወይንም ሁለቴ ተናግሯል: ይህም ሰው በጣም ስለጠየቀው ነው: ፕራብሁፓዳ: “ታድያ አይዘምርም እንዴ?” ዮጊ አምርት ደሳይ:“ይዘምራም:በፀጥታው ግዜ መዘመር የተፈቀደ ነው” ይህም የአምላክን ስም በማወደስ ነው: ይህም ፀጥታን እንደማፍረስ አይቆጠርም: ስለዚህም ይዘምራል: ፕራብሁፓዳ: ፀትታ ማለት አሉባልታ አለማውራት ማለት ነው:ሀሬ ክርሽና መዘመርም ይገባናል: ይህም ፀትታ ማለት ነው: ግዜ ከማባከን እና ይህን አለማዊ ነገር ከማውራት: ሀሬ ክርሽና መዘመር ይገባናል: ይህ ትክክለኛ ነው: ፀጥ ማለት ግን ትክክል አይደለም: ሴንስ የሌለው ነገር መናገር አቁመን ሴንስ ያለው ነገርን መናገር ይገባናል: ዮጊ አምርት ደሳይ:“ይህ ትክክል ነው” ፕራብሁፓዳ: “ፓራም ድርስትቫ ኒቫርታቴ (ብጊ 2 59)ፓራም ድርስትቫ ኑቫርታቴ” አንድ ሰው አሉባልታውን ቢያቆም: ከዚያም “ፓራም” አማላክን “ፓራም ድርስትቫ ኒቫርታቴ” ”ጥሩ ነገር በእጅህ ሲገባ: መጥፎ የያዝከውን ነገር ትጥላለህ“ ”አለማዊ የሆነ ነገር ሁሉ ቆሻሻ ነው“ “ካርማ:ግያና: ዮጋ: እነዚህ ሁሉ አለማዊ ናቸው” “ካርማ: ግያና: ዮጋ: ዮጋ የሚባለው ሁሉ አለማዊ ናቸው”