AM/Prabhupada 0129 - በክርሽና መተማመን ያስፈልጋችኋል፡፡ ምንም ዓይነት እጥረት የለም፡፡

The printable version is no longer supported and may have rendering errors. Please update your browser bookmarks and please use the default browser print function instead.


Lecture on SB 7.6.1 -- Vrndavana, December 2, 1975

ክርሽና እንዲህ ይላል:”ማን ማና ብሃቫ ማድ ብሃክቶ ማድ ማጂ ማም ናማስኩሩ“ (ብጊ 9 34) ይህን እየሰበክን ነው:እዚህ በቤተ መቅደሳችን ለሁሉም እንግዳ “ክርሽና እዚህ ነው” “ሁልግዜም ክርሽናን አስታውስ:ሀሬ ክርሽናንም ዘምር” እንላለን: ከዚያም እንዲህ ማሰብ አለባችሁ:“ሀሬ ክርሽና:ሀሬ ክርሽና” ይህንም መዘመር ክርሽናን ማሰብ ነው ልክ የክርሽናን ስም እንደሰማችሁ:ይህ “ማን ማና” ይባላል: ይህንንስ ማን ያደርገዋል:“ማድ ብሃክታ” የክርሽና ድቮቲም ትሆናላችሁ:ግዜያችሁንም አታባክኑም:“ሀሬ ክርሽና:ሀሬ ክርሽና” ይህም ማለት የሀሬ ክርሽናን ማንትራ በመዘመር ብቻ የክርሽና ድቮቲ መሆን ትችላላችሁ: “ማን ማና ብሃቫ ማድ ብሃክቶ ማድ ያጂ” ድቮቲ የክርሽና ስግደት ለይ ይሰማራል: ሙሉ ቀን እያገለገለ ይገኛል:ሞንገል አራቲ ለክርሽና:ጃፓ መቁጠሪያ ለክርሽና: ምግብ ለክርሽና ማዘጋጀት:የክርሽናን ፕራሳዳም ማቅረብ:እንዲሁም በተለያዩ ነገሮች ያገለግላል: ድቮቲዎች በአለም ላይ በየአገሩ አሉን:ወደ 102 ቅርንጫፎች አሉን:እነዚህም ሁሉ በክርሽና ንቃት ላይ የተሰማሩ ናቸው: ይህ ነው የእኛ ስብከት:ሌላ ስራ የለንም: ምንም ንግድ የለንም ነገር ግን እስከ 25 ላክ ሩፒስ እናጠፋለን: 25 ላክ ሩፒ በየወሩ:ይህንንም ክርሽና እያቀረበ ነው: “ቴሻም ኒትያ ብሂ ዩክታናም ዮጋ ክሼማም ቫሃሚ አሃም” (ብጊ 9 22) በክርሽና ንቃት የዳበራችሁ እና በክርሽና የምትተማመኑ ከሆነ ምንም የሚጎል ነገር አይኖርም: እኔም ይህን የክርሽና ንቃት ማስፋፋት የጀመርኩት:በ40 ሩፒ ነበር:አሁን ግን 40 ከሮር አለን: ታድያ በዚህ አለም በ40 ሩፒ ተነስቶ:በ10 አመት 40 ከሮር የሚያተርፍ ነጋዴ አለ? ሊኖር አይችልም:በዚህም ላይ:10000 ሰው በቀን በቀን ምግብ እየበላ ይገኛል: ይህም የክርሽና ንቃት ነው:“ዮጋ ክሼማም ቫሃሚ አሃም” (ብጊ 9 22) የክርሽና ንቃትህ እንደዳበረ:በእርሱ ተማምነህ አገልግሎትህን በትጉህነት ቀጥል: ክርሽና ታድያ የሚያስፈልግህን ሁሉ ያቀርብልሃል:ሁሉን ነገር: ይህ በተግባር የታየ ነው: ለምሳሌ:ቦምቤይ ያለው መሬቶች እስከ ከሮር ሩፒ ይጠይቃሉ: እኔ ግን ቅርንጫፋችንን ስገዛ:የነበረኝ ገንዘብ 3 ወይንም 4 ላክ ነበር ብዙ ግምትም አድረገን ነበረ:ቢሆንም ልከፍል እንደምችል እርግጠኛ ነበርኩኝ:ምክንያቱም ክርሽና እንደሚረዳኝ ተማምኜ ነበር: የሚበቃ ገንዘን አልነበረንም:ይህም ረጅም ታሪክ ነው:ለመወያየትም አልሻም: ታድያ እንደዚህም:ተግባራዊ ልምድ አለኝ:በክርሽና ከተተማመንን የሚያጥረን ነገር ሊኖር አይችልም: የተፈለገው ነገር ሊገኝ ይችላል:“ቴሻም ኒትያብሂ ዩክታናም” ስለዚህም በክርሽና ንቃት ሁልግዜ ተሰማሩ: ያላችሁም ፍላጎት ሁሉ ሊሟላላችሁ ይችላል: